#AddisAbabaUniversity
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ነፃ እና እራሱን የቻለ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ለማድረግ የተደራጀው ግብረ ሀይል ወደ ስራ መግባቱ ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሥራ አመራር ቦርድ ጋር የግብረ ሃይሉን የሥራ ማስጀመሪያና ትውውቅ መድረክ አካሂደዋል፡፡
መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነጻነት ተጎናፅፈው መስራት እንዲችሉ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቋማዊ ነፃነት ኖሮት መልሶ እንዲደራጅ በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ተቋማዊ ነጻነት መስጠት ከመንግስትም ከማህበረሰቡም ስምምነት የተደረሰበት መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ የለዉጥ ስራ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቃማዊ ነጻነትን ማምጣት ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ተቋማዊ ነጻነት የሚሰጥ መሆኑንም አሳውቀዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነፃነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተጀምሮ ወደ ሌሎች ከፍተኛ ተቋማትም የሚስፋፋ መሆኑም ተገልጿል።
#MoE
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ነፃ እና እራሱን የቻለ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ለማድረግ የተደራጀው ግብረ ሀይል ወደ ስራ መግባቱ ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሥራ አመራር ቦርድ ጋር የግብረ ሃይሉን የሥራ ማስጀመሪያና ትውውቅ መድረክ አካሂደዋል፡፡
መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነጻነት ተጎናፅፈው መስራት እንዲችሉ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቋማዊ ነፃነት ኖሮት መልሶ እንዲደራጅ በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ተቋማዊ ነጻነት መስጠት ከመንግስትም ከማህበረሰቡም ስምምነት የተደረሰበት መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ የለዉጥ ስራ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቃማዊ ነጻነትን ማምጣት ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ተቋማዊ ነጻነት የሚሰጥ መሆኑንም አሳውቀዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ነፃነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተጀምሮ ወደ ሌሎች ከፍተኛ ተቋማትም የሚስፋፋ መሆኑም ተገልጿል።
#MoE
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይበቃል ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ያሉ ዜጎቻችን ፍትህን እንዲያገኙ የሚጠይቅ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን ተመልክተናል። ዘመቻው ሳዑዲ ያሉ ዜጎቻችን እምነበረድ ላይ ለብሰው የሚተኙትን ጥቁር ፌስታል በመልበስ አጋርነት የሚገለፅበት ነው። ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በርካታ ዜጎቻችን እጅግ አስከፊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ይታወቃል። የሳኡዲ አረቢያ መንግስት መሰረታዊ የእስረኛ አያያዝ ህግን እንዲተገብር፣…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update
በሳውዲ ታሳሪዎች ጉዳይ ከንጉሥ ሰልማን ጋር ለመወያየት ለፊታችን ቅዳሜ ቀጠሮ መያዙ ተሰምቷል።
የኢትዮጵያንና የሳውዲ ዐረቢያን ግንኙነት ለማሻሻልና በሳውዲ ታስረው የሚገኙና ወደ ሀገራቸው መመለስ በሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ መፍትሄ እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግስት የላካቸው ከፍተኛ የልዑክ ቡድን የፊታችን ቅዳሜ ከንጉስ ሰልማን ኢብኑ አብዱልአዚዝ ጋር ዉይይት ያደርጋሉ።
በተጨማሪ ልዑኩ በቆታው ከሳውዲ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ሌሎች ባለስልጣናት ጋር ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
የልዑካን ቡድኑ ከሚኒስትሮች፥ከሃይማኖት አባቶች፥ከዉጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በኢትዮ-ሳውዲ ጉዳይ ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ግለሰቦች የተካተቱበት ነው።
ልዑኩ የተላከው የእስረኞችን ችግር ለመፍታትና የሀገራቱን ግንኙነት ለማሻሻል ልዑክ በመላክ ንጉሡን ማናገር እንደሚገባ በሳውዲ ዐረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ባቀረቡት ምክረ ሀሳብ መነሻነት መንግስት ልዑኩ ወደ ሳውዲ እንዲሄድ መንግስት መወሰኑን ነው የተሰማው።
ልዑኩ በአሁኑ ሰዓት በሳውዲ ዐረቢያ ዋና ከተማ በሪያድ ከተማ ይገኛል። የልዑኩ አባላት አስር ሲሆኑ የሚከተሉት ይገኙበታል።
1) አቶ አሕመድ ሺዴ
2) አምባሳደር ሪድዋን ሁሴን
3) ዶ/ር ጄይላን ከድር
4) ፕሮፌሰር አደም ካሚል
5) ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ
6) ቄስ ታጋይ ታደለ
7) አቶ መስፍን ገብሬ
8)አቶ ሀይደር አብደላ
9) አምባሳደር ሌንጮ ባቲ
የኢትዮጵያንና የሳውዲ ዐረቢያን ግንኙነት በተመለከተ ፕሮፌሰር አደም ካሚል በዐረብኛ ቋንቋ ለንጉሡ ገለፃ እንዲያደርጉ በልዑኩ ተመርጠዋል።
ምንጭ፦ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ
@tikvahethiopia
በሳውዲ ታሳሪዎች ጉዳይ ከንጉሥ ሰልማን ጋር ለመወያየት ለፊታችን ቅዳሜ ቀጠሮ መያዙ ተሰምቷል።
የኢትዮጵያንና የሳውዲ ዐረቢያን ግንኙነት ለማሻሻልና በሳውዲ ታስረው የሚገኙና ወደ ሀገራቸው መመለስ በሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ መፍትሄ እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግስት የላካቸው ከፍተኛ የልዑክ ቡድን የፊታችን ቅዳሜ ከንጉስ ሰልማን ኢብኑ አብዱልአዚዝ ጋር ዉይይት ያደርጋሉ።
በተጨማሪ ልዑኩ በቆታው ከሳውዲ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ሌሎች ባለስልጣናት ጋር ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
የልዑካን ቡድኑ ከሚኒስትሮች፥ከሃይማኖት አባቶች፥ከዉጭ ጉዳይ ሚኒስትርና በኢትዮ-ሳውዲ ጉዳይ ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ግለሰቦች የተካተቱበት ነው።
ልዑኩ የተላከው የእስረኞችን ችግር ለመፍታትና የሀገራቱን ግንኙነት ለማሻሻል ልዑክ በመላክ ንጉሡን ማናገር እንደሚገባ በሳውዲ ዐረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ ባቀረቡት ምክረ ሀሳብ መነሻነት መንግስት ልዑኩ ወደ ሳውዲ እንዲሄድ መንግስት መወሰኑን ነው የተሰማው።
ልዑኩ በአሁኑ ሰዓት በሳውዲ ዐረቢያ ዋና ከተማ በሪያድ ከተማ ይገኛል። የልዑኩ አባላት አስር ሲሆኑ የሚከተሉት ይገኙበታል።
1) አቶ አሕመድ ሺዴ
2) አምባሳደር ሪድዋን ሁሴን
3) ዶ/ር ጄይላን ከድር
4) ፕሮፌሰር አደም ካሚል
5) ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ
6) ቄስ ታጋይ ታደለ
7) አቶ መስፍን ገብሬ
8)አቶ ሀይደር አብደላ
9) አምባሳደር ሌንጮ ባቲ
የኢትዮጵያንና የሳውዲ ዐረቢያን ግንኙነት በተመለከተ ፕሮፌሰር አደም ካሚል በዐረብኛ ቋንቋ ለንጉሡ ገለፃ እንዲያደርጉ በልዑኩ ተመርጠዋል።
ምንጭ፦ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ
@tikvahethiopia
#Italy #Ethiopia
#ጣሊያን እና #ኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል የጤና ስርዓቱን ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ።
" በኦሮሚያ ክልል የጤና ስርዓትን ማጠናከር " የተሰኘው ይኸው ፕሮጀክት የጤና ባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት፣ የእናቶችና ህፃናት አገልግሎት ጥራትን ማሻሻል እና ከኤችአይቪ/ኤድስ ጋር የተያያዙ ተግባራትን መደገፍ ያለመ ነው።
በተጨማሪ ፕሮጀክቱ የሎጂስቲክስ አስተዳደርን ማጠናከር ፣ የመረጃ ሥርዓቱን እና የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን (CBHI) ልማትንም ታሳቢ ያደረገ ነው ተብሏል።
ምንጭ፦ በኢትዮጵያ የጣሊያን ኤምባሲ
@tikvahethiopia
#ጣሊያን እና #ኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል የጤና ስርዓቱን ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ።
" በኦሮሚያ ክልል የጤና ስርዓትን ማጠናከር " የተሰኘው ይኸው ፕሮጀክት የጤና ባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት፣ የእናቶችና ህፃናት አገልግሎት ጥራትን ማሻሻል እና ከኤችአይቪ/ኤድስ ጋር የተያያዙ ተግባራትን መደገፍ ያለመ ነው።
በተጨማሪ ፕሮጀክቱ የሎጂስቲክስ አስተዳደርን ማጠናከር ፣ የመረጃ ሥርዓቱን እና የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን (CBHI) ልማትንም ታሳቢ ያደረገ ነው ተብሏል።
ምንጭ፦ በኢትዮጵያ የጣሊያን ኤምባሲ
@tikvahethiopia
#ችሎት
በቀድሞ የብሔራዊ መረጃ ደህንነት ዋና ዳሬክተር በነ አቶ ጌታቸው አሰፋ መዝገብ በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተከሰው የነበሩ 22 ተከሳሾች እያንዳንዳቸው በ30 ሺ ብር ዋስ አሲዘው ከእስር ተፈተው ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጠ።
ብይኑን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ዋስትና ከተፈቀደላቸው መካከል የብሔራዊ መረጃ ደህንኘት ም/ዳሬክተር የነበሩት አቶ ያሬድ ዘሪሁን እና የተቋሙ የፀረሽብር ወንጀሎች መምሪያ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ይገኙበታል።
ፍ/ቤቱ የዓቃቢህግ የዋስትና መቃወሚያን ነጥቦችን ውድቅ በማድረግ በአንድ ዳኛ የድምጽ ተቋውሞ በሁለት ዳኞች አብላጫ ድምጽ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በተባለበት በተሻሻለው አንቀጽ 423 እና አንቀጽ 556 መሰረት ነው 30 ሺህ ብር ዋስ አሲዘው ከስር እንዲፈቱ የፈቀደው።
ፍርድ ቤቱ ዋስትና የተፈቀደላቸው ተከሳሾቹ ከሀገር እንዳይወጡ እገዳ እንዲጣል አዟል።
የዛሬውን ችሎት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራር የሆኑት ፖለቲከኛ ደጀኔ ጣፋ ታድመዋል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
በቀድሞ የብሔራዊ መረጃ ደህንነት ዋና ዳሬክተር በነ አቶ ጌታቸው አሰፋ መዝገብ በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተከሰው የነበሩ 22 ተከሳሾች እያንዳንዳቸው በ30 ሺ ብር ዋስ አሲዘው ከእስር ተፈተው ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጠ።
ብይኑን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
ዋስትና ከተፈቀደላቸው መካከል የብሔራዊ መረጃ ደህንኘት ም/ዳሬክተር የነበሩት አቶ ያሬድ ዘሪሁን እና የተቋሙ የፀረሽብር ወንጀሎች መምሪያ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ይገኙበታል።
ፍ/ቤቱ የዓቃቢህግ የዋስትና መቃወሚያን ነጥቦችን ውድቅ በማድረግ በአንድ ዳኛ የድምጽ ተቋውሞ በሁለት ዳኞች አብላጫ ድምጽ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በተባለበት በተሻሻለው አንቀጽ 423 እና አንቀጽ 556 መሰረት ነው 30 ሺህ ብር ዋስ አሲዘው ከስር እንዲፈቱ የፈቀደው።
ፍርድ ቤቱ ዋስትና የተፈቀደላቸው ተከሳሾቹ ከሀገር እንዳይወጡ እገዳ እንዲጣል አዟል።
የዛሬውን ችሎት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራር የሆኑት ፖለቲከኛ ደጀኔ ጣፋ ታድመዋል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
@tikvahethiopia
#Update
ተቋርጦ የቆየው የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭ ሆነ በስጦታ የማስተላለፍ ውልን ከሰኞ ጥር 23/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚጀምር የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል።
የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭም ሆነ በስጦታ የማስተላለፍ ውልን የማረጋገጥ አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡
አገልግሎቱ ከሰኞ ጥር 23/2014 ዓ.ም ጀምሮ መስጠት እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን አገልግሎቱ ተገልጋዮች በትዕግስት ስለጠበቁት ምስጋና አቅርቧል፡፡
አገልግሎቱን ለማግኘት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት እና የተቋሙን ድረ-ገጽ www.dars.gov.et በመጠቀም ተቋሙ ባዘጋጀው የonline አገልግሎት መጠየቂያ ፎርም በመሙላትና ሲስተሙ የሚሰጠውን የጉዳይ መከታተያ ቁጥር በመያዝ በሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በመቅረብ አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ተናግሯል፡፡
ምንጭ፦ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት / ሸገር ኤፍ ኤም
@tikvahethiopia
ተቋርጦ የቆየው የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭ ሆነ በስጦታ የማስተላለፍ ውልን ከሰኞ ጥር 23/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚጀምር የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል።
የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭም ሆነ በስጦታ የማስተላለፍ ውልን የማረጋገጥ አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡
አገልግሎቱ ከሰኞ ጥር 23/2014 ዓ.ም ጀምሮ መስጠት እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን አገልግሎቱ ተገልጋዮች በትዕግስት ስለጠበቁት ምስጋና አቅርቧል፡፡
አገልግሎቱን ለማግኘት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት እና የተቋሙን ድረ-ገጽ www.dars.gov.et በመጠቀም ተቋሙ ባዘጋጀው የonline አገልግሎት መጠየቂያ ፎርም በመሙላትና ሲስተሙ የሚሰጠውን የጉዳይ መከታተያ ቁጥር በመያዝ በሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በመቅረብ አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ተናግሯል፡፡
ምንጭ፦ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት / ሸገር ኤፍ ኤም
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (ዩኤኢ) ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ጋር በተያያዘ ከኬንያ፣ #ኢትዮጵያ ፣ ታንዛኒያ እና ናይጄሪያ ወደ ሀገሯ የሚገቡ መንገደኞችን አገደች። እግዱ ከታህሳስ 16 ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ነው። እግዱ ወደ ተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ከመምጣታቸው 14 ቀናት በፊት በአራቱ ሀገራት የነበሩ ተጓዦችን እንዳይገቡ ማገድን የሚያካትት ነው። ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ…
#Update
ዩኤኢ ጥላው የነበረው እገዳ ከቅዳሜ ጀምሮ ይነሳል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከ " ኦሚክሮን " ልውጥ የኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ጋር በተያያዘ ከተወሰኑ የአፍሪካ አገራት የሚመጡ መንገደኞች ላይ እገዳ ጥላ እንደነበር ይታወሳል።
እገዳው ከኢትዮጵያ፣ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከኬንያ፣ ከናይጄሪያ እና ከሌሎች ስምንት የአፍሪካ አገራት ወደ ግዛቷ የሚጓዙ ተጓዦችን ያካትት እንደነበር አይዘነጋም።
ይህንን እገዳ ከተጠቀሱት አገራት የሚነሱትን ብቻ ሳይሆን ከጉዟቸው ቀደም ብለው ባሉት 14 ቀናት ውስጥ እዚያ የቆዩትንም ያካትት ነበረ።
አሁን ግን ለሳምንታት ተጥሎ የነበረው እገዳ ከሚቀጥለው #ቅዳሜ አንስቶ እንደሚነሳ በአገሪቱ የብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ቀውሶችንና አደጋዎችን የሚከታተለው ተቋም አስታውቋል።
ነገር ግን ከተለያዩ አፍሪካ አገራት ወደሀገሪቱ የሚጓዙ ሰዎች ከጉዟቸው 48 ሰዓታት በፊት ከበሽታው ነጻ መሆናቸውን የሚያመለክት የኮቪድ-19 ምርመራ ውጤት እና ከሚነሱበት አየር ማረፊያ ፈጣን ምርመራ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ መንገደኞች የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ እንደደረሱ ሌላ የኮቪድ-19 ምርመራ ማድረግ ይገባቸዋል ተብሏል።
@tikvahethiopia
ዩኤኢ ጥላው የነበረው እገዳ ከቅዳሜ ጀምሮ ይነሳል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከ " ኦሚክሮን " ልውጥ የኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ጋር በተያያዘ ከተወሰኑ የአፍሪካ አገራት የሚመጡ መንገደኞች ላይ እገዳ ጥላ እንደነበር ይታወሳል።
እገዳው ከኢትዮጵያ፣ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከኬንያ፣ ከናይጄሪያ እና ከሌሎች ስምንት የአፍሪካ አገራት ወደ ግዛቷ የሚጓዙ ተጓዦችን ያካትት እንደነበር አይዘነጋም።
ይህንን እገዳ ከተጠቀሱት አገራት የሚነሱትን ብቻ ሳይሆን ከጉዟቸው ቀደም ብለው ባሉት 14 ቀናት ውስጥ እዚያ የቆዩትንም ያካትት ነበረ።
አሁን ግን ለሳምንታት ተጥሎ የነበረው እገዳ ከሚቀጥለው #ቅዳሜ አንስቶ እንደሚነሳ በአገሪቱ የብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ቀውሶችንና አደጋዎችን የሚከታተለው ተቋም አስታውቋል።
ነገር ግን ከተለያዩ አፍሪካ አገራት ወደሀገሪቱ የሚጓዙ ሰዎች ከጉዟቸው 48 ሰዓታት በፊት ከበሽታው ነጻ መሆናቸውን የሚያመለክት የኮቪድ-19 ምርመራ ውጤት እና ከሚነሱበት አየር ማረፊያ ፈጣን ምርመራ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ መንገደኞች የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ እንደደረሱ ሌላ የኮቪድ-19 ምርመራ ማድረግ ይገባቸዋል ተብሏል።
@tikvahethiopia
#ሹመት
የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ በቀድሞው ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ያገለገሉትን ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አድርጎ ሾሟል።
አዲሱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ በዛሬው ዕለት በተቋሙ በመገኘት ትውውቅ ያደረጉ ሲሆን በቀጣይ ቀናትም ከአመራሩ እና ከጠቅላላ ሠራተኞች ጋር በመተዋወቅ ስራቸውን በይፋ እንደሚጀምሩ ተገልጿል።
ምንጭ፦ የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት
@tikvahethiopia
የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ በቀድሞው ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ያገለገሉትን ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አድርጎ ሾሟል።
አዲሱ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ በዛሬው ዕለት በተቋሙ በመገኘት ትውውቅ ያደረጉ ሲሆን በቀጣይ ቀናትም ከአመራሩ እና ከጠቅላላ ሠራተኞች ጋር በመተዋወቅ ስራቸውን በይፋ እንደሚጀምሩ ተገልጿል።
ምንጭ፦ የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት
@tikvahethiopia
#AtmafegedYilma
አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ ባደረባቸው ህመም በ86 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
በሚያዚያ 27/1929 ዓ.ም በቀድሞ አጠራር በአርሲ ጠቅላይ ግዛት ጢቾ ከተማ የተወለዱት ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ በ1950 በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የፅህፈት ኮርስ መምህር ሆነው ስራ መጀመራቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ እና በአዲስ ዘመን ጋዜጦች ከአንጋፋው ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ ጋር በአዘጋጅነት የኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣናና በመነን መፅሄት ላይም አገልግለዋል።
በደራሲነት የብደል ካሳ የተሰኘ ልብወለድ ፣ የአቤቶ ኢያሱ አነሳስ እና አወዳደቅ ፣ የህይወቴ ሚስጥር (የ50ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላቸው ማስታወሻ) መፅሀፍትን አሳትመዋል።
ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ በኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ውስጥም አገልግለዋል።
ባለትዳር እና የ4 ወንዶች እና የአንዲት ሴት ልጅ አባት ነበሩ።
ስርዓተ ቀብራቸው ነገ 8 ሰዓት ሃያት በሚገኘው ሰአሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን እንደሚፈፀም ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።
ፎቶ : የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር
@tikvahethiopia
አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ ባደረባቸው ህመም በ86 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
በሚያዚያ 27/1929 ዓ.ም በቀድሞ አጠራር በአርሲ ጠቅላይ ግዛት ጢቾ ከተማ የተወለዱት ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ በ1950 በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የፅህፈት ኮርስ መምህር ሆነው ስራ መጀመራቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ እና በአዲስ ዘመን ጋዜጦች ከአንጋፋው ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ ጋር በአዘጋጅነት የኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣናና በመነን መፅሄት ላይም አገልግለዋል።
በደራሲነት የብደል ካሳ የተሰኘ ልብወለድ ፣ የአቤቶ ኢያሱ አነሳስ እና አወዳደቅ ፣ የህይወቴ ሚስጥር (የ50ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላቸው ማስታወሻ) መፅሀፍትን አሳትመዋል።
ጋዜጠኛ እና ደራሲ አጥናፍሰገድ ይልማ በኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ውስጥም አገልግለዋል።
ባለትዳር እና የ4 ወንዶች እና የአንዲት ሴት ልጅ አባት ነበሩ።
ስርዓተ ቀብራቸው ነገ 8 ሰዓት ሃያት በሚገኘው ሰአሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን እንደሚፈፀም ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።
ፎቶ : የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray , #Mekelle📍 በዛሬው ዕለት የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ከባለፈው መስከረም ወር ወዲህ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የመጀመሪያውን የህክምና ቁሳቁስ ድጋፎችን ማድረስ መቻሉን አሳውቋል። አስፈላጊ መድሃኒቶችን ያካተተው የአስቸኳይ ህክምና ቁሳቁሶች አቅርቦት በክልሉ በጣም ለተጎዱ የጤና ተቋማት ይደርሳል ተብሏል። ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ተጨማሪ በረራዎችን በማዘጋጀት…
#Tigray , #Mekelle 📍
የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በረራ ዛሬ (ጥር 19 ቀን 2014 ዓ.ም) ሁለተኛውን ዙር የአስቸኳይ ህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ ትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ አድርሷል፡፡
#ICRC
@tikvahethiopia
የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በረራ ዛሬ (ጥር 19 ቀን 2014 ዓ.ም) ሁለተኛውን ዙር የአስቸኳይ ህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ ትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ አድርሷል፡፡
#ICRC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዩኤኢ ጥላው የነበረው እገዳ ከቅዳሜ ጀምሮ ይነሳል። የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከ " ኦሚክሮን " ልውጥ የኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ጋር በተያያዘ ከተወሰኑ የአፍሪካ አገራት የሚመጡ መንገደኞች ላይ እገዳ ጥላ እንደነበር ይታወሳል። እገዳው ከኢትዮጵያ፣ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከኬንያ፣ ከናይጄሪያ እና ከሌሎች ስምንት የአፍሪካ አገራት ወደ ግዛቷ የሚጓዙ ተጓዦችን ያካትት እንደነበር አይዘነጋም። ይህንን…
" የዱባይ በረራ ቅዳሜ ይጀምራል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመጪው ጥር 21 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጦ የነበረውን በረራ ወደ ዱባይ እንደሚጀምር ዛሬ አሳውቋል።
ተጓዦች የጉዞ ምዝገባ ለመያዝ ይህንን 👉 https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app ማስፈንጠሪያ መጠቀም እንደሚችሉ አየር መንገዱ ጨምሮ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመጪው ጥር 21 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጦ የነበረውን በረራ ወደ ዱባይ እንደሚጀምር ዛሬ አሳውቋል።
ተጓዦች የጉዞ ምዝገባ ለመያዝ ይህንን 👉 https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app ማስፈንጠሪያ መጠቀም እንደሚችሉ አየር መንገዱ ጨምሮ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ... የሀገሪቱን ጥቅም የሚያስቀድም ምክንያታዊ ድርድር ይካሄዳል ብለውናል " - አቶ መስፍን ተገኑ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ መንግስታቸው ከህወሓት ጋር የተኩስ አቁምን በተመለከተ እንደሚደራደር መናገራቸውን አሶስየትድ ፕሬስ አንድ የዳያስፖራ ቡድን ሊቀ መንበርን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። የዳያስፖራ ቡድን አባላት ከጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ባካሄዱት የግል ውይይት ከትግራይ ኃይሎች ጋር ተኩስ አቁምን…
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለድርድር ምን አሉ ?
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህ መግለጫ ላይ ከሰሞኑን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከዳይስፖራ አባላት ጋር በዝግ በመከሩበት ወቅት ከህወሓት ጋር ስለሚደረግ ድርድር ተናግረዋል በተባለው ጉዳይ አስተያየት ሰጥተዋል።
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ፦
" ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከ ' ህወሓት ' እንደራደር ብለዋል ብሎ አንድ ሰው ተናገረ ያ ሰው የተናገረውንም አንድ ጋዜጠኛ ሪፖርት አደረገ ነው የተባለው ...እኛ ግን Officially በዚህ ረገድ የተባለ ነገር የለም ፤ አልተባለም።
ይሄ ድርጅት አሁንም በህግ designated የሆነ terrorist ድርጅት ነው።
የተባለው ግልፅ ነው፤ ለሰላም ተብሎ እኮ ኢትዮጵያ አንድ ብቻዋን አንድ ጊዜ ከትግራይ የመጣችበት ሁኔታ አለ። ነገር ግን ከ terrorist ድርጅት ጋር እንነጋገራል የሚል አቋም የተገለፀበት አጋጣሚ የለም። "
ከቀናት በፊት የአሜሪካን ኢትዮጵያውያን ህዝባዊ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀመንበር መስፍን ተገኑ ለአሜሪካው የዜና ወኪል አሶሼትድ ፕሬስ (ኤፒ) የዳያስፖራ ቡድን አባላት ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ባካሄዱት የግል ውይይት ወቅት ከህወሓት ጋር ተኩስ አቁምን የተመለከተ ድርድር ይካሄዳል ሲሉ ዶ/ር ዐቢይ እንደነገሯቸው ገልፀው ነበር፤ ዜና ወኪሉም የሳቸውን (አቶ መስፍን ተገኑ) ቃል ዋቢ አድርጎ ነበር ዜናውን ያሰራጨው።
የቡድኑ አባላት ከዶ/ር ዐቢይ ጋራ ባለፈው ቅዳሜ ዕለት ለ5 ሰዓታት መነጋገራቸውን የገለጹት አቶ መስፍን ተገኑ ዶ/ር ዐቢይ የሀገሪቱን ጥቅም የሚያስቀድም ምክንያታዊ ድርድር ይካሄዳል ማለታቸውን ነበር ለአሶሼትድ ፕሬስ የገለፁት።
@tikvahethiopia
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህ መግለጫ ላይ ከሰሞኑን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከዳይስፖራ አባላት ጋር በዝግ በመከሩበት ወቅት ከህወሓት ጋር ስለሚደረግ ድርድር ተናግረዋል በተባለው ጉዳይ አስተያየት ሰጥተዋል።
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ፦
" ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከ ' ህወሓት ' እንደራደር ብለዋል ብሎ አንድ ሰው ተናገረ ያ ሰው የተናገረውንም አንድ ጋዜጠኛ ሪፖርት አደረገ ነው የተባለው ...እኛ ግን Officially በዚህ ረገድ የተባለ ነገር የለም ፤ አልተባለም።
ይሄ ድርጅት አሁንም በህግ designated የሆነ terrorist ድርጅት ነው።
የተባለው ግልፅ ነው፤ ለሰላም ተብሎ እኮ ኢትዮጵያ አንድ ብቻዋን አንድ ጊዜ ከትግራይ የመጣችበት ሁኔታ አለ። ነገር ግን ከ terrorist ድርጅት ጋር እንነጋገራል የሚል አቋም የተገለፀበት አጋጣሚ የለም። "
ከቀናት በፊት የአሜሪካን ኢትዮጵያውያን ህዝባዊ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀመንበር መስፍን ተገኑ ለአሜሪካው የዜና ወኪል አሶሼትድ ፕሬስ (ኤፒ) የዳያስፖራ ቡድን አባላት ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ባካሄዱት የግል ውይይት ወቅት ከህወሓት ጋር ተኩስ አቁምን የተመለከተ ድርድር ይካሄዳል ሲሉ ዶ/ር ዐቢይ እንደነገሯቸው ገልፀው ነበር፤ ዜና ወኪሉም የሳቸውን (አቶ መስፍን ተገኑ) ቃል ዋቢ አድርጎ ነበር ዜናውን ያሰራጨው።
የቡድኑ አባላት ከዶ/ር ዐቢይ ጋራ ባለፈው ቅዳሜ ዕለት ለ5 ሰዓታት መነጋገራቸውን የገለጹት አቶ መስፍን ተገኑ ዶ/ር ዐቢይ የሀገሪቱን ጥቅም የሚያስቀድም ምክንያታዊ ድርድር ይካሄዳል ማለታቸውን ነበር ለአሶሼትድ ፕሬስ የገለፁት።
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA😷
የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 7,758
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 456
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 11
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 1,334
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 316
ዛሬ ፣ ትላንት እና ከትላንት በስቲያ አጠቃላይ 1,407 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ 38 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
@tikvahethiopia
የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 7,758
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 456
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 11
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 1,334
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 316
ዛሬ ፣ ትላንት እና ከትላንት በስቲያ አጠቃላይ 1,407 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ 38 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
@tikvahethiopia
#MostInfluentialYoungAfricans
#አቫንስ_ሚዲያ_አፍሪካ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመትን ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር የነበሩት ፊልሰን አብዱላሂ፣ ሳሙኤል አለማየሁ እንዲሁም ቢታኒያ ሉሉ ብርሃኑን በ2021 ከ100 ተፅእኖ ፈጣሪ የአፍሪካ ወጣቶች ዝርዝር ውስጥ አካቷቸዋል።
አቫንስ ሚዲያ 100ዎቹ 2021 ተፅእኖ ፈጣሪ የአፍሪካ ወጣቶች በተለያየ መስክ የተሰማሩ መሆናቸውን እንዲሁም ከ100ዎቹ መካከል 52ቱ ወንዶች 48ቱ ደግሞ ሴቶች መሆናቸውን ገልጿል።
የተመረጡት 100 ወጣቶች 32 የአፍሪካ ሀገራትን እንደሚወክሉ አሳውቋል።
በዝርዝሩ ውስጥ ከተካተቱ መካከል የጎረቤታችን ሀገር ሱዳን ኢንቬስተር ኢስላም ኤልቢቲ የምትገኝበት ሲሆን በእግር ኳሱ ዓለም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁት ሰኢዶ ማኔ፣ ሪያድ ማሃሬዝ ፣ ኩሉባሊ ፤ ፔየርኤምሪክ ኦባምያንግ ፣ ሞሀመድ ሳላ ይገኙበታል።
ምንጭ፦ https://t.co/SfVdxF0qD0
@tikvahethiopia
#አቫንስ_ሚዲያ_አፍሪካ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመትን ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር የነበሩት ፊልሰን አብዱላሂ፣ ሳሙኤል አለማየሁ እንዲሁም ቢታኒያ ሉሉ ብርሃኑን በ2021 ከ100 ተፅእኖ ፈጣሪ የአፍሪካ ወጣቶች ዝርዝር ውስጥ አካቷቸዋል።
አቫንስ ሚዲያ 100ዎቹ 2021 ተፅእኖ ፈጣሪ የአፍሪካ ወጣቶች በተለያየ መስክ የተሰማሩ መሆናቸውን እንዲሁም ከ100ዎቹ መካከል 52ቱ ወንዶች 48ቱ ደግሞ ሴቶች መሆናቸውን ገልጿል።
የተመረጡት 100 ወጣቶች 32 የአፍሪካ ሀገራትን እንደሚወክሉ አሳውቋል።
በዝርዝሩ ውስጥ ከተካተቱ መካከል የጎረቤታችን ሀገር ሱዳን ኢንቬስተር ኢስላም ኤልቢቲ የምትገኝበት ሲሆን በእግር ኳሱ ዓለም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁት ሰኢዶ ማኔ፣ ሪያድ ማሃሬዝ ፣ ኩሉባሊ ፤ ፔየርኤምሪክ ኦባምያንግ ፣ ሞሀመድ ሳላ ይገኙበታል።
ምንጭ፦ https://t.co/SfVdxF0qD0
@tikvahethiopia