TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
58.9K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነስቷል ?

" የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነስቷል " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መረጃ ነው።

ለ6 ወራት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ እንዲያጥር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ውሳኔ አሳልፋል።

በዚህም አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የ6 ወር ጊዜው ሳይጠናቀቅ ጊዜውን የማሳጠር ስልጣን ያለው ህ/ተ/ም/ቤት የአዋጁን ተፈጻሚነት ቀሪ እንዲያደርገው #የሚጠይቅ የውሳኔ ሃሳብ በማፅደቅ ለምክር ቤቱ እንዲተላለፍ ተወስኗል።

ጉዳዩ ይህ ሆኖ ሳለ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደተነሳ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

ኢትዮጵያ አሁንም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር ናት።

@tikvahethiopia