TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ጄነራል መሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ አዲስ አበባ ሲደርሱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ እና የብሄራዊ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎና የልዑካን ቡድናቸው በኢትዮጵያ በሚኖረው ቆይታ…
#GeneralDagallo
ጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር እንዲሁም ከሌሎች አመራሮች ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል።
ጄነራሉ ባጋሩት ፎቶ : ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ጋር መገናኘታቸውን ያሳያል።
ሄሜቲ ጉብኝቱን በተመለከተ ፥ " ... አዲስ አበባን በመጎብኘቴ እና የዚህችን ውብ ሀገር መሪዎች በወንድማማችነት መንፈስ በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ። ይህም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ጥልቀት እና ጥንካሬ ያረጋግጣል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
ጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር እንዲሁም ከሌሎች አመራሮች ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል።
ጄነራሉ ባጋሩት ፎቶ : ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፣ ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ጋር መገናኘታቸውን ያሳያል።
ሄሜቲ ጉብኝቱን በተመለከተ ፥ " ... አዲስ አበባን በመጎብኘቴ እና የዚህችን ውብ ሀገር መሪዎች በወንድማማችነት መንፈስ በማግኘቴ ደስተኛ ነኝ። ይህም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ጥልቀት እና ጥንካሬ ያረጋግጣል " ብለዋል።
@tikvahethiopia