“ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት አስደሳች ነው " - ዲያን ካስተሊክ
የሳፋሪኮም፣ ቮዳኮም፣ ቮዳፎን፣ ሱሚቶሞ እና ሲዲሲ ጥምረት ልዑካንና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አመራሮቻችን ከኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣን ዳይሬክተር ጀነራል ኢንጂነር ባልቻ ጋር ተወያይተዋል።
ከጥምረቱ አባላት አንዱ የሆነው የቮዳኮም ግሩፕ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲያን ካስተሊክ፣ ባለሥልጣን መስሪያቤቱ እስካሁን ላደረገው ያልተቋረጠ ድጋፍ እና መልካም ግንኙነት ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ሚስተር ዲያን ፥ “ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት አስደሳች ነው፡፡ እንደ ቮዳኮም ሌሎች አገራት ያለንን ልምድ ማካፈል መቻላችንም ያስደስተናል፡፡ ቮዳኮም ለዲጂታል አካታችነት እና ለፋይናንስ አገልግሎቶች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ በመሆኑ በኢትዮጵያ ከቴሌኮም አቅርቦት በተጨማሪ ሌሎች እገዛዎችን ለማድረግ እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል።
ኢ/ር ባልቻ ሬባ የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ወደ አገር ውስጥ ለሥራ የሚያስፈልጉትን ቁሳቁስ በማስገባትና የባለድርሻ አካላት ግንኙነትን በማመቻቸት ሳፋሪኮም ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ማቅረብ እንዲችል እገዛ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡
የሳፋሪኮም የውጪ ጉዳዮች እና ሬጉላቶሪ ኃላፊ ማቲው ሃርቬ-ሃሪሰን፣ ድርጅታችን የፈቃድ ግዴታዎችን እና መመሪያዎችን በመከተል በተቻለው ፍጥነት የኔትዎርክ አቅርቦቱን ለማቀላጠፍ አፅንዖት ሰጥቶ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
ሚስተር ማቲው የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን በጉምሩክ እና ኢምፖርት ሂደቶች ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
ውይይቱ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሚገኝበትን የዝግጅት ደረጃ እና በቀጣይ የሚሠሩ ሥራዎችን በመግለጽ ተጠናቋል፡፡
#ሳፋሪኮምኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
የሳፋሪኮም፣ ቮዳኮም፣ ቮዳፎን፣ ሱሚቶሞ እና ሲዲሲ ጥምረት ልዑካንና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አመራሮቻችን ከኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣን ዳይሬክተር ጀነራል ኢንጂነር ባልቻ ጋር ተወያይተዋል።
ከጥምረቱ አባላት አንዱ የሆነው የቮዳኮም ግሩፕ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲያን ካስተሊክ፣ ባለሥልጣን መስሪያቤቱ እስካሁን ላደረገው ያልተቋረጠ ድጋፍ እና መልካም ግንኙነት ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ሚስተር ዲያን ፥ “ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት አስደሳች ነው፡፡ እንደ ቮዳኮም ሌሎች አገራት ያለንን ልምድ ማካፈል መቻላችንም ያስደስተናል፡፡ ቮዳኮም ለዲጂታል አካታችነት እና ለፋይናንስ አገልግሎቶች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ በመሆኑ በኢትዮጵያ ከቴሌኮም አቅርቦት በተጨማሪ ሌሎች እገዛዎችን ለማድረግ እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል።
ኢ/ር ባልቻ ሬባ የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ወደ አገር ውስጥ ለሥራ የሚያስፈልጉትን ቁሳቁስ በማስገባትና የባለድርሻ አካላት ግንኙነትን በማመቻቸት ሳፋሪኮም ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ማቅረብ እንዲችል እገዛ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡
የሳፋሪኮም የውጪ ጉዳዮች እና ሬጉላቶሪ ኃላፊ ማቲው ሃርቬ-ሃሪሰን፣ ድርጅታችን የፈቃድ ግዴታዎችን እና መመሪያዎችን በመከተል በተቻለው ፍጥነት የኔትዎርክ አቅርቦቱን ለማቀላጠፍ አፅንዖት ሰጥቶ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
ሚስተር ማቲው የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን በጉምሩክ እና ኢምፖርት ሂደቶች ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
ውይይቱ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሚገኝበትን የዝግጅት ደረጃ እና በቀጣይ የሚሠሩ ሥራዎችን በመግለጽ ተጠናቋል፡፡
#ሳፋሪኮምኢትዮጵያ
@tikvahethiopia