TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DrDanielBekele

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ከሰሞኑን ከአል ዓይን የአማርኛው አገልግሎት ጋር ሰፋ ያለ ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።

ዶ/ር ዳንኤል በዚሁ ቃለ ምልልስ በርካታ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተጠይቀው ዝርዝር ምላሽ ሰጥተዋል።

በቃለ ምልልሱ ምን ምን ጉዳዮች ተነሱ ?

- በቅርቡ ስለተሸለሙት የጀርመን አፍሪካ ሽልማት።

- ኢሰመኮ ከዚህ ቀደም ሪፖርት ሲያደርጋቸው የነበሩ የመብት ጥሰቶችን ተከትሎ የመጣ ተጠያቂነት ይኖር ስለመሆኑ ?

- ከትግራዩ ጦርነት ጋር በተያያዘ ተፈጽመዋል የተባሉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ከተመድ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ጋር በጋራ ስለተሰራው ምርመራ። የምርመራውን ውጤት የህወሃት ቡድን ያልተቀበለበት ምክንያት።

- በምርመራዎቹ እና በሌሎች የኢሰመኮ ስራዎች ላይ ከመንግስት አካላት ጫና ይደረግባችሁ ነበር ? ወይ ተብለው ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

- ህወሃት ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ለመንግስት ያደላሉ እያለ ስለሚያቀርበው ቅሬታ ምላሽ ሰጥተዋል።

- የጣምራ ምርመራ በአፋርና አማራ ክልሎች ይቀጥል እንደሆነ ተጠይቀው መልሰዋል።

- ምርመራ አድረጋለሁ ብሎ የነበረው የአፍሪካ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከምን ደርሶ ይሆን ?

- በኢትዮጵያ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን ተከትሎ ስለሚገለፀው በተለይ ደግሞ የትግራይ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እስር ጉዳይ አስተያየት ሰጥተዋል።

- ኢትዮጵያ አሁን ስላለችበት ሁኔታ ምልከታቸውን አጋርተዋል።

ያንብቡ : https://am.al-ain.com/article/ehrc-chief-says-there-is-no-interference-from-government-in-its-work

@tikvahethiopia