#StateofEmergencySomalia
ሶማሊያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች። ሀገሪቱ በከፍተኛ ድርቅ መጠቃቷን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጀችው።
እየተባባሰ በመጣው ወቅታዊ የድርቅ ሁኔታ ላይ የሃገሪቱን ካቢኔ ለአስቸኳይ ስብሰባ የጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መሃመድ ሮብል አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አውጀዋል፡፡
“ሃገራችን በድንገተኛ ሰብዓዊ አደጋ ላይ ትገኛለች” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያጋጠመውን አስከፊ ድርቅ ሰላባዎች እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ለማድረግ በዝግጅት ላይ ባለችው ጎረቤት አገር ሶማሊያ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ገደማ ሰዎች ለከፋ ድርቅ ተጋልጠዋል፡፡
በርካቶች ለችግር መዳረጋቸውን የተመድ የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ማስተባበሪያ አስታውቋል፡፡
በሶማሊያ ባለፉት ሶስት የዝናብ ወቅቶች ዝናብ ያልዘነበ ሲሆን በተለይም ጁባ እና ሸበሌ ወንዞች የውሃ መጠናቸው በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ የድርቁን ደረጃ እንዳባባሰው ድርጅቱ አክሏል፡፡
የድርቅ መጠኑ በተለይም ከቀጣዩ ታህሳስ ወር ጀምሮ እስከ መጋቢት ድረስ እንደሚባባስ የገለጸው ድርጅቱ ተጎጂዎችን ለመርዳት የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ መሆኑንም ጠቅሷል፡፡
Credit : Al AIN News
@tikvahethiopia
ሶማሊያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች። ሀገሪቱ በከፍተኛ ድርቅ መጠቃቷን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጀችው።
እየተባባሰ በመጣው ወቅታዊ የድርቅ ሁኔታ ላይ የሃገሪቱን ካቢኔ ለአስቸኳይ ስብሰባ የጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መሃመድ ሮብል አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አውጀዋል፡፡
“ሃገራችን በድንገተኛ ሰብዓዊ አደጋ ላይ ትገኛለች” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያጋጠመውን አስከፊ ድርቅ ሰላባዎች እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ለማድረግ በዝግጅት ላይ ባለችው ጎረቤት አገር ሶማሊያ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ገደማ ሰዎች ለከፋ ድርቅ ተጋልጠዋል፡፡
በርካቶች ለችግር መዳረጋቸውን የተመድ የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ማስተባበሪያ አስታውቋል፡፡
በሶማሊያ ባለፉት ሶስት የዝናብ ወቅቶች ዝናብ ያልዘነበ ሲሆን በተለይም ጁባ እና ሸበሌ ወንዞች የውሃ መጠናቸው በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ የድርቁን ደረጃ እንዳባባሰው ድርጅቱ አክሏል፡፡
የድርቅ መጠኑ በተለይም ከቀጣዩ ታህሳስ ወር ጀምሮ እስከ መጋቢት ድረስ እንደሚባባስ የገለጸው ድርጅቱ ተጎጂዎችን ለመርዳት የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ መሆኑንም ጠቅሷል፡፡
Credit : Al AIN News
@tikvahethiopia