TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በአቶ #ዳውድ_ኢብሳ የሚመራው ኦነግ ከኦዴፓና ከኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ።በሃገር ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የኦነግ ታጣቂ ወደ ካምፕ ለማስገባት የተሰራው ስራ ላይ የማጠቃለያ ሪፖርት ዛሬ ቀርቧል። ሪፖርቱ በመንግስትና በኦነግ የዕርቀ ሰላም ኮሚቴና የሃገር ሽማግሌዎች አማካኝነት፥ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ማዕከላዊ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እና የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በተገኙበት ነው የቀረበው።

ከሪፖርቱ በኋላ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የኦነግ አመራሮች፥ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነትና አንድነት ለማረጋገጥ በጋራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል። ኦነግ የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚሰራቸውን ስራዎች #እንደሚደግፍም ሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ተናግረዋል። አያይዘውም ከዚህ በኋላ ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ሰራዊት እንደማይኖርም ገልፀዋል።

Via #FBC
ፎቶ፦ #ጃዋር_መሃመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia