TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.08K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Bahirdar : በባህርዳር ከተማ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህገ-ወጥ ሽጉጥ እንዲሁም የብሬን፣ የክላሸና የሽጉጥ ጥይቶች በቁጥጥር ስር ዋለ። በባህር ዳር ከተማ ልዩ ቦታው ዳግማዊ ምንሊክ ክፍለ ከተማ ማርዘነብ ቀበሌ በተባለው ስፍራ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ፦ - 51 ትልቁ ቱርክ ሰራሽ ህገ-ወጥ ሽጉጥ፣ - 2ሺ 1መቶ የብሬን ጥይት፣ - 69 የክላሽ ጥይት እንዲሁም 222 የሽጉጥ…
#Bahridar : በባህር ዳር ከተማ ከግለሰብ ቤት ውስጥ ህገወጥ የጦር መሳሪያ ተያዘ።

በዳግማዊ ሚኒሊክ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ማር ዘነብ ቀበሌ ሲቱ ዋርካ አካባቢ በአንድ ተጠርጣሪ ቤት ፖሊስ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ ፦
• 3676 የክላሽ ጥይት፣
• 1288 የመትረየስ ጥይት፣
• 3 ክላሽንኮፍ ጠመንጃ እና 20 የተለያዩ ሽጉጦች ከመሰል ጥይቶቻቸው ጋር መያዙን የ9ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ክፍል አሳውቋል።

ፖሊስ ህገወጥ የጦር መሳሪያውን በድንገተኛ ፍተሻ ሊይዝ የቻለው ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሆኑን ገልጿል።

Credit : አማራ ፖሊስ

@tikvahethiopia
#Bahridar : በባህር ዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘውን የአባይ ድልድይ የግንባታ ብረት የሰረቁት ግለሰቦች በቁጥጥር ዋሉ።

ከ50 ዓመት በላይ አግልግሎት የሰጠው የባህርዳር ከተማ አባይ ድልድይ በእድሜ ብዛት ወቅቱን የሚመጥን የትራፊክ ፍሰትን ማስተናገድ ተቸግሯል።

ይህንን ለመቅረፍ በከፍተኛ በጀት አዲሱ ድልድይ በአባይ ወንዝ ላይ እየተገነባ ነው።

የባህር ዳር ከተማ ፖሊስ ፥ "ይህንን የህዝብ ሀብት ለግል ጥቅም ማዋል የፈለጉ ስግብግብ ግለሰቦች የተለያዩ የስርቆት ወንጀል መፈፀማቸውን ተረጋግጧል" ብሏል።

በአካባቢው ቅኝት ሲያደርጉ የነበሩት የሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ባልደረቦች በ12/02/2014 ዓ/ም ምሽት የድልድዩን የግንባታ ብረት ሰርቀው ሊያጓጉዙ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርምራ እያጣራ ይገኛል ሲልም አክሏል።

አጠቃላይ በስርቆቱ የተሳተፉ እና በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች ግን በፖሊስ መረጃ ላይ አልተገለፀም።

የባህር ዳር ፖሊስ ፥ " ክልሉ የህልውና ትግል ላይ ባለበት በዚህ ወቅት የሀገርንና የህዝብን ሃብት በመዝረፍ ለግል ጥቅም ለማዋል የሚጥሩትን የውስጥ ባንዳዎች ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ህብረተሰቡ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል" ሲል ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia