#Masha በማሻ ከተማ የእንቅስቃሴ ገደብ ተጣለ።
በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ማሻ ከተማ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሉን የመቅደላ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አሳውቋል።
ገደቡ የተጣለው የሀገሪቱን እና የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ለህዝቡ ደህንነት ሲባል መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ የእንቅስቃሴ ገደቡን በተመለከተ በሰጠው ማብራሪያ በማሻ ከተማ ከዛሬ ጀምሮ ሞተርና ባጃጅ ከምሽቱ 1 ሰዓት በኃላ እንዲሁም ማንኛውም ሰው ከ2 ሰዓት በኃላ መንቀሳቀስ እንደማይችል አሳስቧል።
የእንቅስቃሴ ገደቡ ከደሴ-ማሻ የሚሰሩ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎችን አይጨምርም ተብሏል።
ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት እንዲሁም በድንገተኛ ችግር ምክንያት ካልሆነ በስተቀር የእንቅስቃሴ ገደቡን የሚተላለፍ ማንኛውም አካል ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ፖሊስ አስጠንቅቆ ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ማሻ ከተማ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሉን የመቅደላ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አሳውቋል።
ገደቡ የተጣለው የሀገሪቱን እና የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ለህዝቡ ደህንነት ሲባል መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ የእንቅስቃሴ ገደቡን በተመለከተ በሰጠው ማብራሪያ በማሻ ከተማ ከዛሬ ጀምሮ ሞተርና ባጃጅ ከምሽቱ 1 ሰዓት በኃላ እንዲሁም ማንኛውም ሰው ከ2 ሰዓት በኃላ መንቀሳቀስ እንደማይችል አሳስቧል።
የእንቅስቃሴ ገደቡ ከደሴ-ማሻ የሚሰሩ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎችን አይጨምርም ተብሏል።
ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት እንዲሁም በድንገተኛ ችግር ምክንያት ካልሆነ በስተቀር የእንቅስቃሴ ገደቡን የሚተላለፍ ማንኛውም አካል ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ፖሊስ አስጠንቅቆ ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia