TIKVAH-ETHIOPIA
" ስንት ሰው ሲሞት፣ ስንት ሰው ሲያልቅ ነው የዓለም ማህበረሰብ ወለጋ ላይ ሰው እያለቀ ነው ብሎ ድምፁን የሚያሰማው ? " - የምስራቅ ወለጋ [ሀሮ አዲስ ዓለም] ነዋሪዎች በምስቅራ ወለጋ [ሀሮ አዲስ ዓለም] በሸኔ ታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ ሰዎች እየተገደሉ መሆኑን ነዋሪዎች ገልፀዋል። በምስራቅ ወለጋ ባሉ ወረዳዎች እየተፈፀመ ባለው ጥቃት የትኛውም ኃይል ሊከላከልላቸው እንዳልገባ የሚናገሩት ነዋሪዎች…
#EastWollega : በኪራሙ ወረዳ ሀሮ ቀበሌ ባለፉት ተከታታይ ቀናት በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች ተገድለዋል፣ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ተፈናቅለውም ተሰደዋል።
ይህ እየሆነ ያለው በአካባቢው በታጣቂዎች እየተፈፀመ ባለ ጥቃት መሆኑን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
አንድ የአካባቢው ነዋሪው በሰሞኑ ጥቃት ኃይለኛ እልቂት መድረሱን ተናግረው ፤ ነዋሪዎች ንብረታቸው ተዘርፎ ወደ ኪረሙ፣ ወደ ጊዳ ፣ ነቀምት መሰደዳቸው ጠቁመዋል፤ ችግሩን የሚያበርድም አካል አልተገኘም ብለዋል።
የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ በሰጡት ቃል ፥ በህ/ተ/ም/ቤት ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው "ሸኔ" ከህወሓት ጋር አንድ መሆኑን ካወጀ ለኃላ የብሄር ግጭት ለማስነሳት የተለያዩ አካባቢዎች ጥቃት እየፈፀመ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
"ሸኔ" ባለፉት 3 ቀናትም ኪረሙ ወረዳ ላይ ጥቃት መፈፀሙን እና ንፁሃን መገደላቸውን ገልፀዋል።
በተጨማሪ ከሌላ አካባቢ የመጣ ሳይሆን ፤ በዛው አካባቢ የሚንቀሳቀስ የ "ሸኔ" ተፃራሪ "ፅንፈኛ" ቡድን አለ ያሉ ሲሆን የሚሰራው ድርጊት ከ "ሸኔ" ጋር ይጋራል አብሮ የሚኖረውን ማህበረሰብ ለይቶ በማጥቃት የፖለቲካ አጀንዳ ለማግኘት የሚንቀሳቀስ የ "ሽፍታ" ቡድን ነው ብለዋል።
ኃላፊው #ለኢቲቪ በሰጡት ቃል ደግሞ ይህ የ "ሸፈተ" ቡድን ያሉት ኃይል የአማርኛ ተናጋሪ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ሁለቱ አካላት ናቸው በንፁሃን ላይ ጥቃት ያደረሱት የሚሉት አቶ ኃይሉ ፥ ከሰሞኑ በነበረው ጥቃት 15 ሰዎች መገደላቸውን አሳውቀዋል፤ ድርጊቱ የብሄር ግጭት ለመቀስቀስ ነበር ሲሉ ተናግረዋል።
" የሰሞኑን ጥቃት ማንነት መሰረት አድርጎ ተፈፀመ የሚለውም ሊስተካከል ይገባል " ሲሉም የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አቶ ኃይሉ አዱኛ ሲናግሩ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia
ይህ እየሆነ ያለው በአካባቢው በታጣቂዎች እየተፈፀመ ባለ ጥቃት መሆኑን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
አንድ የአካባቢው ነዋሪው በሰሞኑ ጥቃት ኃይለኛ እልቂት መድረሱን ተናግረው ፤ ነዋሪዎች ንብረታቸው ተዘርፎ ወደ ኪረሙ፣ ወደ ጊዳ ፣ ነቀምት መሰደዳቸው ጠቁመዋል፤ ችግሩን የሚያበርድም አካል አልተገኘም ብለዋል።
የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ በሰጡት ቃል ፥ በህ/ተ/ም/ቤት ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው "ሸኔ" ከህወሓት ጋር አንድ መሆኑን ካወጀ ለኃላ የብሄር ግጭት ለማስነሳት የተለያዩ አካባቢዎች ጥቃት እየፈፀመ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
"ሸኔ" ባለፉት 3 ቀናትም ኪረሙ ወረዳ ላይ ጥቃት መፈፀሙን እና ንፁሃን መገደላቸውን ገልፀዋል።
በተጨማሪ ከሌላ አካባቢ የመጣ ሳይሆን ፤ በዛው አካባቢ የሚንቀሳቀስ የ "ሸኔ" ተፃራሪ "ፅንፈኛ" ቡድን አለ ያሉ ሲሆን የሚሰራው ድርጊት ከ "ሸኔ" ጋር ይጋራል አብሮ የሚኖረውን ማህበረሰብ ለይቶ በማጥቃት የፖለቲካ አጀንዳ ለማግኘት የሚንቀሳቀስ የ "ሽፍታ" ቡድን ነው ብለዋል።
ኃላፊው #ለኢቲቪ በሰጡት ቃል ደግሞ ይህ የ "ሸፈተ" ቡድን ያሉት ኃይል የአማርኛ ተናጋሪ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ሁለቱ አካላት ናቸው በንፁሃን ላይ ጥቃት ያደረሱት የሚሉት አቶ ኃይሉ ፥ ከሰሞኑ በነበረው ጥቃት 15 ሰዎች መገደላቸውን አሳውቀዋል፤ ድርጊቱ የብሄር ግጭት ለመቀስቀስ ነበር ሲሉ ተናግረዋል።
" የሰሞኑን ጥቃት ማንነት መሰረት አድርጎ ተፈፀመ የሚለውም ሊስተካከል ይገባል " ሲሉም የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አቶ ኃይሉ አዱኛ ሲናግሩ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia