TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Tole

በምዕራብ ወለጋ " ቶሌ ቀበሌ " ለሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖች የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ ተደረገላቸው።

ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የጋምቤላ ፣ የቄለምና ምዕራብ ወለጋ ፣ የአሶሳና የደቡብ ሱዳን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምዕራብ ወለጋ በቶሌ ቀበሌ ተፈናቅለው የሚገኙ  ወገኖችን በሥፍራው በመገኘት የጎበኙ ሲሆን የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

በቀበሌው ተፈናቅለው የሚገኙ ወገኖች መንፈሳዊ አገልግሎት የሚያገኙበት የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ለመገንባትም ብፁዕነታቸው የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጣቸውም ተገልጿል።

በሚቀጥሉት ቀናት ለምዕራብ ወለጋ ሰራተኞች፣ በሥሩ ለሚገኙ ሃያ ወረዳ  ሊቃነ ካህናት፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሥልጠና ይሰጣል ፤ የወረዳዎች ሪፖርትም በማድመጥ በስራ አፈፃፀማቸው ዙሪያ ውይይት ይካሄዳል ተብሏል።

ከዚሁ መርሐ ግብር መጠናቀቅ በኋላም ፤ በዞኑ #የዘላቂ_ሰላም_ውይይት እንደሚደረግ ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
👍610108👎35🙏33😢8😱7