ደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።
የደ/ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ13ኛው ዙር የ2013 ዓ/ም ተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት እያከናወነ ነው።
ዛሬ የመጀመሪያው ዙር ምርቃት (በዋናው ግቢ) ሲሆን ነገ ደግሞ በቡሬ ካምፓስ ተማሪዎች ይመረቃሉ።
በአጠቃላይ ምን ያህል ተማሪዎች ይመረቃሉ ?
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን በመደበኛው፣ በማታና በክረምት
• ሴት 1193
• ወንድ 2122 በድምሩ ከ3,315 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ
በሁለተኛ ዲግሪ ፦
• 143 ሴቶችና
• 254 ወንዶች በድምሩ 397 ተማሪዎችን በአጠቃላይ 3712 ምሩቃንን በዋናው ግቢ ሃዲስ አለማየሁ የጉባዔ አዳራሽ እና ሃምሌ 18/2013 ዓ/ም በቡሬ ካምፓስ ይመረቃሉ።
ከዩኒቨርሲቲው በተገኘው መረጃ በዋናው ግቢ 2,905 ተማሪዎች ናቸው የሚመረቁት።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮችን : @tikvahuniversity
የደ/ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ13ኛው ዙር የ2013 ዓ/ም ተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት እያከናወነ ነው።
ዛሬ የመጀመሪያው ዙር ምርቃት (በዋናው ግቢ) ሲሆን ነገ ደግሞ በቡሬ ካምፓስ ተማሪዎች ይመረቃሉ።
በአጠቃላይ ምን ያህል ተማሪዎች ይመረቃሉ ?
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን በመደበኛው፣ በማታና በክረምት
• ሴት 1193
• ወንድ 2122 በድምሩ ከ3,315 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ
በሁለተኛ ዲግሪ ፦
• 143 ሴቶችና
• 254 ወንዶች በድምሩ 397 ተማሪዎችን በአጠቃላይ 3712 ምሩቃንን በዋናው ግቢ ሃዲስ አለማየሁ የጉባዔ አዳራሽ እና ሃምሌ 18/2013 ዓ/ም በቡሬ ካምፓስ ይመረቃሉ።
ከዩኒቨርሲቲው በተገኘው መረጃ በዋናው ግቢ 2,905 ተማሪዎች ናቸው የሚመረቁት።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮችን : @tikvahuniversity
ቻይና በአሜሪካ ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ እየጣለች ነው።
ቻይና በርከት ባሉ የአሜሪካ ባለሥልጣናት እና ተቋማት ላይ ማዕቀብ እየጣለች ትገኛለች። ሀገሪቱ ማዕቀብ እየጣለች የምትገኘው አሜሪካ በሆንግ ኮንግ ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ ለመጣሏ የመልስ ምት ነው።
አሜሪካ በሆንግ ኮንግ ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ ጥላ የነበረው በዜጎች ላይ የጸጥታ ኃይሎች በሚወስዱት እርምጃ እጃቸው አለበት በሚል ነበር።
አሁን ቻይና ማዕቀብ ከጣለችባቸው የአሜሪካ ባለሥልጣናት መካከል የቀድሞው የንግድ ዘርፍ ጸሐፊ ዊልበር ሮስ በዋ ዋንኝነት ይጠቀሳሉ።
ከዊልበር ሮስ በተጨማሪ የመብት ተሟጋቹ ሂውማን ራይትስ ዋች የቻይና ቅርንጫፍ ዳይሬክተር ሶፊ ሪቻርድሰን ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል።
የቻይና እና አሜሪካ የምጣኔ ሀብትና ደኅንነት ኮሚሽን ኃላፊ ካሮሊን ባርቶሎሜው፣ የዓለም አቀፉ የሪፐብሊካን ተቋም አመራር አዳም ኪንግ ላይም ማዕቀብ ተጥሏል።
የአሁኑ የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዌንዲ ሸርማን በጥቂት ቀናት ውስጥ ቻይናን ይጎበኛሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው ፥ በዚህ ወቅት ነው እንግዲ ቻይና በአሜሪካ ባለስጣናት ላይ ማዕቀብ መጣል የጀመረችው።
የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ የሆኑት ጄን ሳኪ አሜሪካ በቻይና ማዕቀብ "አትበገርም" ብለዋል።
NB : ቻይና ከዚህ ቀደም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስተር ማይክ ፖምፕዮን ጨምሮ 27 የትራምፕ ዘመን አመራሮች ላይ ማዕቀብ መጣሏ ይታወሳል።
መረጃው ከቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
ቻይና በርከት ባሉ የአሜሪካ ባለሥልጣናት እና ተቋማት ላይ ማዕቀብ እየጣለች ትገኛለች። ሀገሪቱ ማዕቀብ እየጣለች የምትገኘው አሜሪካ በሆንግ ኮንግ ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ ለመጣሏ የመልስ ምት ነው።
አሜሪካ በሆንግ ኮንግ ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ ጥላ የነበረው በዜጎች ላይ የጸጥታ ኃይሎች በሚወስዱት እርምጃ እጃቸው አለበት በሚል ነበር።
አሁን ቻይና ማዕቀብ ከጣለችባቸው የአሜሪካ ባለሥልጣናት መካከል የቀድሞው የንግድ ዘርፍ ጸሐፊ ዊልበር ሮስ በዋ ዋንኝነት ይጠቀሳሉ።
ከዊልበር ሮስ በተጨማሪ የመብት ተሟጋቹ ሂውማን ራይትስ ዋች የቻይና ቅርንጫፍ ዳይሬክተር ሶፊ ሪቻርድሰን ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል።
የቻይና እና አሜሪካ የምጣኔ ሀብትና ደኅንነት ኮሚሽን ኃላፊ ካሮሊን ባርቶሎሜው፣ የዓለም አቀፉ የሪፐብሊካን ተቋም አመራር አዳም ኪንግ ላይም ማዕቀብ ተጥሏል።
የአሁኑ የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዌንዲ ሸርማን በጥቂት ቀናት ውስጥ ቻይናን ይጎበኛሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው ፥ በዚህ ወቅት ነው እንግዲ ቻይና በአሜሪካ ባለስጣናት ላይ ማዕቀብ መጣል የጀመረችው።
የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ የሆኑት ጄን ሳኪ አሜሪካ በቻይና ማዕቀብ "አትበገርም" ብለዋል።
NB : ቻይና ከዚህ ቀደም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስተር ማይክ ፖምፕዮን ጨምሮ 27 የትራምፕ ዘመን አመራሮች ላይ ማዕቀብ መጣሏ ይታወሳል።
መረጃው ከቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በመሰረታዊ ውትድርና ያሰለጠናቸውን 2ኛ ዙር ምልምል ወታደሮች እያስመረቀ ይገኛል።
ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወቅት ለውትድርና ሙያ ብቁ የሚያደርጋቸውን የመሰረታዊ ውትድርና ስልጠና ወስደው ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።
በምርቃት ስነስርቱ ላይ የተገኙት የምድር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ ለተመራቂ ወታደሮቹ ይሰጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።
ጀኔራል መኮንኖች፣ የትምህርት ቤቱ አዛዥ ኮ/ል አዲሱ ተርፋሳ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል ፤ ከሀገር መከላከያ እና ለኢዜአ እንደተገኘው መረጃ።
NB : የሁርሶ የሰላም ማስከበር ማዕከል በምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኝ እና አንጋፋ ከሚባሉት ማሰልጠኛዎች መካከል ተጠቃሽ ነው።
@tikvahethiopia
የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በመሰረታዊ ውትድርና ያሰለጠናቸውን 2ኛ ዙር ምልምል ወታደሮች እያስመረቀ ይገኛል።
ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወቅት ለውትድርና ሙያ ብቁ የሚያደርጋቸውን የመሰረታዊ ውትድርና ስልጠና ወስደው ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።
በምርቃት ስነስርቱ ላይ የተገኙት የምድር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ ለተመራቂ ወታደሮቹ ይሰጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።
ጀኔራል መኮንኖች፣ የትምህርት ቤቱ አዛዥ ኮ/ል አዲሱ ተርፋሳ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል ፤ ከሀገር መከላከያ እና ለኢዜአ እንደተገኘው መረጃ።
NB : የሁርሶ የሰላም ማስከበር ማዕከል በምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኝ እና አንጋፋ ከሚባሉት ማሰልጠኛዎች መካከል ተጠቃሽ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tokyo2020 #Taekwondo ሰለሞን ቱፋ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አልፏል ? እጅግ ተጠባቂው የቶኪዮ ኦሎምፒክ ውድድር ትላንት ተጀምሯል። ኢትዮጵያ ሀገራችን በውድድሩ ከምትካፈልበት የውድድር ዘርፎች አንዱ የወርልድ ቴኳንዶ ውድድር ነው። ኢትዮጵያ በውድድሩ በሰለሞን ቱፋ የተወከለች ሲሆን ከሰዓታት በፊት በተደረገው ውድድር የሀገራችን ልጅ ሰለሞን ቱፋ የጃፓኑን ተጋጣሚው ሰርጅዮ ሱዙኪ በመርታት ወደ ሩብ…
ሰለሞን ቱፋ ለ ነሀስ 🥉 ሜዳሊያ ይወዳደራል !
የጃፓኑን ተጋጣሚው ሰርጅዮ ሱዙኪ በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜው ያለፈው ሰለሞን ቱፋ ደምሴ በቱኒዚያው ተፎካካሪው በነጥብ ልዩነት ቢሸነፍም በተሻለ ነጥብ ወደ ቀጣዩ ዙር በማለፍ ተጫማሪ ውድደሩን ያደርጋል።
ሰለሞን ቱፋ ዛሬ ከ ቀኑ 7:15 ላይ ከ ሩሲያዊው አርታሞኖቭ ሚኪሀሊ ጋር የሚፋለም ይሆናል።
ሰለሞን ቱፋ የነሀስ ሜዳልያ ለማግኘት በሚደረገው ፉክክር ከሩሲያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተወዳዳሪ አርታሞኖቭ ሚካዪል ጋር የሚፋለም ይሆናል፡፡
መልካም እድል ለሀገራችን ልጅ ሰለሞን ቱፋ !
Pic Credit : Hawariyaw Petros
ስፖርታዊ ጉዳዮች : @tikvahethsport
የጃፓኑን ተጋጣሚው ሰርጅዮ ሱዙኪ በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜው ያለፈው ሰለሞን ቱፋ ደምሴ በቱኒዚያው ተፎካካሪው በነጥብ ልዩነት ቢሸነፍም በተሻለ ነጥብ ወደ ቀጣዩ ዙር በማለፍ ተጫማሪ ውድደሩን ያደርጋል።
ሰለሞን ቱፋ ዛሬ ከ ቀኑ 7:15 ላይ ከ ሩሲያዊው አርታሞኖቭ ሚኪሀሊ ጋር የሚፋለም ይሆናል።
ሰለሞን ቱፋ የነሀስ ሜዳልያ ለማግኘት በሚደረገው ፉክክር ከሩሲያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተወዳዳሪ አርታሞኖቭ ሚካዪል ጋር የሚፋለም ይሆናል፡፡
መልካም እድል ለሀገራችን ልጅ ሰለሞን ቱፋ !
Pic Credit : Hawariyaw Petros
ስፖርታዊ ጉዳዮች : @tikvahethsport
#ItsMyDam🇪🇹
ዳይስፖራው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚያደርግበት ድረገፅ ይፋ ሆነ።
በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴው ግድብ ባሉበት ሆነው ድጋፍ የሚያሰባስብቡበት ድረገፅን መሰረት ያደረገ ፕላትፎርም ይፋ ሆኗል።
ይህ ፕላትፎርም www.mygerd.com ድረገፅ በመግባት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው።
በድረ-ገፁ አማካይነት የሚሰባሰበው ድጋፍ በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በዘመን ባንክ ለግድቡ ግንባታ ወደተከፈተው የውጭ ምንዛሬ አካውንት እንዲገባ የሚደረግ ሲሆን የሚውለውም ለታለመበት ዓላማ ብቻ ይሆናል ተብሏል።
ከዚህ ቀደም ለህዳሴው ግድብ ኢትዮጵያውያን በ8100 በኩል ድጋፍ ማድረግ የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቶ በ3 የተለያዩ ዙሮች ከ252 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል፤ ግድቡ ግንባታው ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ በቦንድና በልገሳ ድጋፍ ተደርጓል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
@tikvahethiopia
ዳይስፖራው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚያደርግበት ድረገፅ ይፋ ሆነ።
በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴው ግድብ ባሉበት ሆነው ድጋፍ የሚያሰባስብቡበት ድረገፅን መሰረት ያደረገ ፕላትፎርም ይፋ ሆኗል።
ይህ ፕላትፎርም www.mygerd.com ድረገፅ በመግባት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው።
በድረ-ገፁ አማካይነት የሚሰባሰበው ድጋፍ በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በዘመን ባንክ ለግድቡ ግንባታ ወደተከፈተው የውጭ ምንዛሬ አካውንት እንዲገባ የሚደረግ ሲሆን የሚውለውም ለታለመበት ዓላማ ብቻ ይሆናል ተብሏል።
ከዚህ ቀደም ለህዳሴው ግድብ ኢትዮጵያውያን በ8100 በኩል ድጋፍ ማድረግ የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቶ በ3 የተለያዩ ዙሮች ከ252 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል፤ ግድቡ ግንባታው ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ በቦንድና በልገሳ ድጋፍ ተደርጓል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሰለሞን ቱፋ ለ ነሀስ 🥉 ሜዳሊያ ይወዳደራል ! የጃፓኑን ተጋጣሚው ሰርጅዮ ሱዙኪ በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜው ያለፈው ሰለሞን ቱፋ ደምሴ በቱኒዚያው ተፎካካሪው በነጥብ ልዩነት ቢሸነፍም በተሻለ ነጥብ ወደ ቀጣዩ ዙር በማለፍ ተጫማሪ ውድደሩን ያደርጋል። ሰለሞን ቱፋ ዛሬ ከ ቀኑ 7:15 ላይ ከ ሩሲያዊው አርታሞኖቭ ሚኪሀሊ ጋር የሚፋለም ይሆናል። ሰለሞን ቱፋ የነሀስ ሜዳልያ ለማግኘት በሚደረገው ፉክክር ከሩሲያ…
#Tokyo2020 #Ethiopia🇪🇹
ሰለሞን ቱፋ በመጨረሻም የሶስተኛ ዙር ጨዋታውን ተሸንፎ ለ ነሀስ ሜዳልያ ከሚደረገው ውድድር ውጪ ሆኗል።
በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያን በመወከል በ58 ኪሎ ግራም በ ወርልድ ቴኳንዶ የተሳተፈው ሰለሞን ቱፋ በመጀመሪያ ጨዋታው የጃፓኑን ተጋጣሚው ሱዙኪ ሰርጂዮን በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜ ያለፈ ሲሆን በሩብ ፍፃሜው በቱኒዚያው ተፎካካሪው ተሸንፏል።
ቱኒዚያዊው ሞሀመድ ካሊል 32 ለ 9 በሆነ የ ነጥብ ልዩነት ሰለሞን ቱፋን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍፃሜው አልፏል ።
ሰለሞን ቱፋ በ2ቱ ጨዋታዎች በሰበሰበው ነጥብ የ ነሀስ ሜዳለያ ለማግኘት በሚደረገው ፉክክር ከ ሩሲያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተወዳዳሪ አርታሞኖቭ ሚካዬል ጋር ጨዋታ አድርጎ በድምር ነጥብ 27 ለ 5 ተሸንፎ የቶክዮ ኦሊምፒክ ውድድር ጨዋታዎቹን አጠናቋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ በኦሎምፒክ ታሪካችን በወርልድ ቴክዋንዶ እንድንወከል ላደረገን እና በውድድሩም ጥሩ ተጋድሎ በማድረግ መፎካከር በቻለው ሰለሞን ቱፋ 🇪🇹 ኮርተናል።
[#HawaryawPetros]
ስፖርታዊ ጉዳዮች @tikvahethsport
ሰለሞን ቱፋ በመጨረሻም የሶስተኛ ዙር ጨዋታውን ተሸንፎ ለ ነሀስ ሜዳልያ ከሚደረገው ውድድር ውጪ ሆኗል።
በቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያን በመወከል በ58 ኪሎ ግራም በ ወርልድ ቴኳንዶ የተሳተፈው ሰለሞን ቱፋ በመጀመሪያ ጨዋታው የጃፓኑን ተጋጣሚው ሱዙኪ ሰርጂዮን በመርታት ወደ ሩብ ፍፃሜ ያለፈ ሲሆን በሩብ ፍፃሜው በቱኒዚያው ተፎካካሪው ተሸንፏል።
ቱኒዚያዊው ሞሀመድ ካሊል 32 ለ 9 በሆነ የ ነጥብ ልዩነት ሰለሞን ቱፋን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍፃሜው አልፏል ።
ሰለሞን ቱፋ በ2ቱ ጨዋታዎች በሰበሰበው ነጥብ የ ነሀስ ሜዳለያ ለማግኘት በሚደረገው ፉክክር ከ ሩሲያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተወዳዳሪ አርታሞኖቭ ሚካዬል ጋር ጨዋታ አድርጎ በድምር ነጥብ 27 ለ 5 ተሸንፎ የቶክዮ ኦሊምፒክ ውድድር ጨዋታዎቹን አጠናቋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ በኦሎምፒክ ታሪካችን በወርልድ ቴክዋንዶ እንድንወከል ላደረገን እና በውድድሩም ጥሩ ተጋድሎ በማድረግ መፎካከር በቻለው ሰለሞን ቱፋ 🇪🇹 ኮርተናል።
[#HawaryawPetros]
ስፖርታዊ ጉዳዮች @tikvahethsport
#AddisAbaba
#ሐምሌ_19 የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ይከበራል።
ከመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም (ቤተመንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል) በደረሰን መልዕክት የፊታችን ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል በዓል በደመቀ መልኩ ይከበራል።
"በዓመት 2 ጊዜ ታህሳስ እና ሐምሌ 19 ብቻ" እንደሚነግስ የተገለፀልን ሲሆን የዛሬ ዓመት በኮሮና ወረርሽኝ እና በአንዳንድ ወቅታዊ ጉዳዮች ምክንያት ለምዕመናን ውስን ሆኖ ነበር የተከበረው።
በዚህ ዓመት ግን ምዕመናን ራሳቸውን ጠብቀው ከተሟላ ፓርኪንግ ጋር እንዲሁም መንገዱም ስለተከፈተ መጥተው ማክበር ይችላሉ ተብሏል።
በዚህ አጋጣሚ አንዳንድ ገዳሙ እንደተዘጋ ተደርጎ የሚናፈሱ መረጃዎች ፍፁም #ሀሰተኛ ናቸው።
የ124 ዘመን እድሜ ያለው የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በዳግማዊ ንጉሰ ነገሥት አፄ ምንሊክ መታነጹ ይነገራል።
አድራሻ ፦ ታላቁ ቤተመንግሥት (አንድነት ፓርክ) ጎን።
@tikvahethiopia
#ሐምሌ_19 የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ይከበራል።
ከመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም (ቤተመንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል) በደረሰን መልዕክት የፊታችን ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል በዓል በደመቀ መልኩ ይከበራል።
"በዓመት 2 ጊዜ ታህሳስ እና ሐምሌ 19 ብቻ" እንደሚነግስ የተገለፀልን ሲሆን የዛሬ ዓመት በኮሮና ወረርሽኝ እና በአንዳንድ ወቅታዊ ጉዳዮች ምክንያት ለምዕመናን ውስን ሆኖ ነበር የተከበረው።
በዚህ ዓመት ግን ምዕመናን ራሳቸውን ጠብቀው ከተሟላ ፓርኪንግ ጋር እንዲሁም መንገዱም ስለተከፈተ መጥተው ማክበር ይችላሉ ተብሏል።
በዚህ አጋጣሚ አንዳንድ ገዳሙ እንደተዘጋ ተደርጎ የሚናፈሱ መረጃዎች ፍፁም #ሀሰተኛ ናቸው።
የ124 ዘመን እድሜ ያለው የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በዳግማዊ ንጉሰ ነገሥት አፄ ምንሊክ መታነጹ ይነገራል።
አድራሻ ፦ ታላቁ ቤተመንግሥት (አንድነት ፓርክ) ጎን።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ItsMyDam🇪🇹 ዳይስፖራው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚያደርግበት ድረገፅ ይፋ ሆነ። በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴው ግድብ ባሉበት ሆነው ድጋፍ የሚያሰባስብቡበት ድረገፅን መሰረት ያደረገ ፕላትፎርም ይፋ ሆኗል። ይህ ፕላትፎርም www.mygerd.com ድረገፅ በመግባት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው። በድረ-ገፁ አማካይነት የሚሰባሰበው ድጋፍ በብሔራዊ…
#ItsMyDam🇪🇹
ዛሬ ይፋ በተደረገው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማድረጊያ የድረገፅ ፕላትፎርም ዜጎች ድጋፍ ማድረግ ጀምረዋል።
Mygerd.com የተሰኘው ድጋፍ ማድረጊያ ድረገፅ ይፋ በተደረገ በደቂቃዎች ውስጥ 36 ሰዎች ባደረጉት ልገሳ ስለማድረጋቸው ታውቋል። በዚህም 1,899 የአሜሪካ ዶላር ሊሰበሰብ ችሏል።
አምስትሰዎች ለሌሎች በማስተዋወቅ ዘመቻውን ስለመቀላቀላቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወጣው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
ዛሬ ይፋ በተደረገው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማድረጊያ የድረገፅ ፕላትፎርም ዜጎች ድጋፍ ማድረግ ጀምረዋል።
Mygerd.com የተሰኘው ድጋፍ ማድረጊያ ድረገፅ ይፋ በተደረገ በደቂቃዎች ውስጥ 36 ሰዎች ባደረጉት ልገሳ ስለማድረጋቸው ታውቋል። በዚህም 1,899 የአሜሪካ ዶላር ሊሰበሰብ ችሏል።
አምስትሰዎች ለሌሎች በማስተዋወቅ ዘመቻውን ስለመቀላቀላቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወጣው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
#Hawassa
ሃምሌ 19 በድምቀት ለሚከበረው የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል ዝግጅት እየተደረገ ነው።
በበዓሉ ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከሀይማኖት አባቶችና የበዓሉ ዝግችት ኮሚቴ ጋር ከቀናት በፊት ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ ትኩረት አድርጎ የነበረው የእንግዶች አቀባበል፣ የትራፊክ ፍሰት ማስተናበር፣ የፀጥታ ሁኔታ እና ሌሎች በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ነበር።
ዛሬ ጥዋት ደግሞ የሐዋሳ ከተማ እና የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ከለብ ደጋፊዎች የንግስ በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ የጽዳት ዘመቻ አካሂደዋል።
የቅዱስ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪ መላከ ሠላም አባ ኃ/ጊዮርጊስ ማህጽነት የሁለቱ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።
በአሉ እስኪጠናቀቅ እንግዶችን በመቀበል በማስተናገድ የተለመደውን ትበብር እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ዛሬ ከተካሄደው የፅዳት ዘመቻ ጋር በተያያዘ በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታ ዳንኤል በሰጡት አስተያየት "የጽዳት ዘመቻ አንድነትን መከባባርን የሚያመለክት ነው" ሲሉ ገልፀዋል።
Photo Credit : Hawassa City Administration (3)
ተጨማሪ ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
ሃምሌ 19 በድምቀት ለሚከበረው የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል ዝግጅት እየተደረገ ነው።
በበዓሉ ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ከሀይማኖት አባቶችና የበዓሉ ዝግችት ኮሚቴ ጋር ከቀናት በፊት ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ ትኩረት አድርጎ የነበረው የእንግዶች አቀባበል፣ የትራፊክ ፍሰት ማስተናበር፣ የፀጥታ ሁኔታ እና ሌሎች በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ነበር።
ዛሬ ጥዋት ደግሞ የሐዋሳ ከተማ እና የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ከለብ ደጋፊዎች የንግስ በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ የጽዳት ዘመቻ አካሂደዋል።
የቅዱስ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪ መላከ ሠላም አባ ኃ/ጊዮርጊስ ማህጽነት የሁለቱ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።
በአሉ እስኪጠናቀቅ እንግዶችን በመቀበል በማስተናገድ የተለመደውን ትበብር እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ዛሬ ከተካሄደው የፅዳት ዘመቻ ጋር በተያያዘ በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታ ዳንኤል በሰጡት አስተያየት "የጽዳት ዘመቻ አንድነትን መከባባርን የሚያመለክት ነው" ሲሉ ገልፀዋል።
Photo Credit : Hawassa City Administration (3)
ተጨማሪ ፎቶ ፦ ፋይል
@tikvahethiopia
"እናቴ በጭንቀት ታማለች"
ከሳምንታት በፊት የታሰሩት የአውሎ ሚዲያ ጋዜጠኞች እና ሰራተኞች እስካሁን ያሉበትን እንደማያውቁ ቤተሰቦቻቸው ዛሬ በስልክ ሪፖርት አድርገውልናል።
እስር ላይ ካሉ የአውሎ ሰራተኞች መካከል የአንድ ታሳሪ የቤተሰብ አባል የሆነች እንስት ጋዜጠኞቹና የሚዲያ ሰራተኞቹ የት እንዳሉ ቤተሰብ ባለማወቁ ለከፍተኛ ጭንቀት መዳረጋቸውን ገልፃለች።
ቤተሰብ ስላለበት ሁኔታ እንደሚከተለው አስረድታለች፦
" ... ያሉበት አይታወቅም ይህ ነው አስጨናቂው ነገር ፤ ቢታወቅ እና ብንጠይቃቸው መልካም ነበር። ማንም ሰው ሊታሰር ይችላል ምንም ችግር የለውም፤ መንግስት የያዘው ነገር ከሆነ አያስፈራም። ምግብ እስከሰጠን፣ ልብስ እስከሰጠን ድረስ፣ መጎብኘት እስከቻልን ድረስ፣ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብታቸው እስከተጠበቀ ድረስ ችግር የለውም መንግስት የራሱን መልስ እስከማሰጥ እንጠብቃለን። ነገር ግን ያሉበትን ባለመታወቁ ለቤተሰብ ከፍተኛ ጭንቅ ነው። ለምሳሌ እናቴ ታማለች። የሌሎቹም ልጆች ያሏቸው ልጆቻው ያልቀሳሉ፣ እናት አባቶችም ያለቅሳሉ እነሱ ያሉበት ባለመታወቁ የብዙዎቹ ቤተሰቦች ህይወት ተመሰቃቅሏል"
በታሰሩ በነጋታው ወደ ፌዴራል ፖሊስ ሄደው እንዳገኟቸው እዛ እንደሆኑ ታውቆ እንደነበር የገለፀችልን የታሳሪ ቤተሰብ አባሏ፣ "ፖሊስ አጣርቶ ይለቃቸዋል በሚል ቤተሰብ ወደቤት ተመለሰ በነጋታው ግን የሉም ተባልን"
የት ሄዱ? የት ተወሰዱ? ስለሚለው ጉዳይ ምንም ነገር አይገልፁልንም፤ ፈተናቸዋልም ብለውናል ፤ ፈተናቸዋል ማለታቸው ደግሞ ይበልጥ ቤተሰብን ጭንቀት ውስጥ ከቶታትል ስትል አስተድታለች።
መንግስት ስላሉበት ሁኔታ ለቤተስቦች ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቃለች።
* በጋዜጠኞቹ እና ሰራተኞቹ ጉዳይ አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ ለፍ/ቤት ቀርቦ ለሰኞ ተቀጥሯል።
@tikvahethiopia
ከሳምንታት በፊት የታሰሩት የአውሎ ሚዲያ ጋዜጠኞች እና ሰራተኞች እስካሁን ያሉበትን እንደማያውቁ ቤተሰቦቻቸው ዛሬ በስልክ ሪፖርት አድርገውልናል።
እስር ላይ ካሉ የአውሎ ሰራተኞች መካከል የአንድ ታሳሪ የቤተሰብ አባል የሆነች እንስት ጋዜጠኞቹና የሚዲያ ሰራተኞቹ የት እንዳሉ ቤተሰብ ባለማወቁ ለከፍተኛ ጭንቀት መዳረጋቸውን ገልፃለች።
ቤተሰብ ስላለበት ሁኔታ እንደሚከተለው አስረድታለች፦
" ... ያሉበት አይታወቅም ይህ ነው አስጨናቂው ነገር ፤ ቢታወቅ እና ብንጠይቃቸው መልካም ነበር። ማንም ሰው ሊታሰር ይችላል ምንም ችግር የለውም፤ መንግስት የያዘው ነገር ከሆነ አያስፈራም። ምግብ እስከሰጠን፣ ልብስ እስከሰጠን ድረስ፣ መጎብኘት እስከቻልን ድረስ፣ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብታቸው እስከተጠበቀ ድረስ ችግር የለውም መንግስት የራሱን መልስ እስከማሰጥ እንጠብቃለን። ነገር ግን ያሉበትን ባለመታወቁ ለቤተሰብ ከፍተኛ ጭንቅ ነው። ለምሳሌ እናቴ ታማለች። የሌሎቹም ልጆች ያሏቸው ልጆቻው ያልቀሳሉ፣ እናት አባቶችም ያለቅሳሉ እነሱ ያሉበት ባለመታወቁ የብዙዎቹ ቤተሰቦች ህይወት ተመሰቃቅሏል"
በታሰሩ በነጋታው ወደ ፌዴራል ፖሊስ ሄደው እንዳገኟቸው እዛ እንደሆኑ ታውቆ እንደነበር የገለፀችልን የታሳሪ ቤተሰብ አባሏ፣ "ፖሊስ አጣርቶ ይለቃቸዋል በሚል ቤተሰብ ወደቤት ተመለሰ በነጋታው ግን የሉም ተባልን"
የት ሄዱ? የት ተወሰዱ? ስለሚለው ጉዳይ ምንም ነገር አይገልፁልንም፤ ፈተናቸዋልም ብለውናል ፤ ፈተናቸዋል ማለታቸው ደግሞ ይበልጥ ቤተሰብን ጭንቀት ውስጥ ከቶታትል ስትል አስተድታለች።
መንግስት ስላሉበት ሁኔታ ለቤተስቦች ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቃለች።
* በጋዜጠኞቹ እና ሰራተኞቹ ጉዳይ አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ ለፍ/ቤት ቀርቦ ለሰኞ ተቀጥሯል።
@tikvahethiopia
#AFAR
"...እነሱ ለሚፈፅሙት እያንዳንዱ ድርጊት አፀፋዊ ምላሽ መስጠት ለኛ በጣም ቀላል ነው ፤ ይህንንም እናደርገዋለን" - አቶ አወል አርባ
ትግራይ ክልልን ከአፋር ክልልና አማራ ክልል በሚያዋስኑ አካባቢዎች ስላለው መሬት ላይ ያለ ሁኔት በግልፅ በዝርዝር ባይታወቅም አሁንም ድረስ ወታደራዊ ግጭቶች ስለመኖራቸው የሚገልፁ ጥቆማዎች አሉ።
በአካባቢው ላይ ባለው ግጭት ምክንያት ሺዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተፈናቅለዋል።
የአፋር ክልል ፕሬዜዳንት የሆኑት አቶ አወል አርባ በወቅታዊ የክልሉ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።
አቶ አወል አርባ ፥ በአሁን ሰዓት ህወሓት አጠቃላይ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ዓላማ አንግቦ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል።
"እኛ ኢትዮጵያን ከመራን ኢትዮጵያዊ ነን፤ ኢትዮጵያን ካልመራን ግን ኢትዮጵያዊ አይደለንም ስለዚህ ኢትዮጵያን አፍርሰን እራሳችን መንግስት እንሆናለን የሚል ዓላማ ይዘው የመጡት አሁን ሳይሆን በ1968 ጫካ በነበሩበት ወቅት የፃፉት መፅሃፍ በግልፅ ምስክ እንደሆነና ዶክመቱም በታሪክ ድርሳናት እጅ ይገኛል" ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ አወል ፥ ሽብርተኛ ተብሎ ለተፈረጀው ህወሓት ለሚፈፅመው እያንዳንዱ ድርጊት አፀፋዊ ምላሽ መስጠት እንችላለን ፤ መንገዶችን በህፃናት ለማዘጋት ሞክረዋል፤ እነሱ ላደረጉት ተግባር አፀፋ መስጠት ለኛ ቀላል ነው ይህንንም እናደርገዋለን ብለዋል።
የአፋርን ህዝብ ሰብዓዊነት የጎደለው ትግባርን በመፈፀም አንበረክከዋለሁ ማለት የማታሰብ ነው ያሉት ፕሬዜዳንቱ አፋር በታሪኩ የሽንፈት ታሪክ አጋጥሞት አያውቅም በአሸባሪነት የተፈረጀውን 'ህወሓት' በተባበረ ክንድ እንፋለመዋለን ፤ ዳግም ላይመለስ የሚገባውን ዋጋ በሚገባው ቋንቋ እንሰጠዋለን ሲሉ ዝተዋል ።
ያንብቡ : telegra.ph/Afar-07-24
@tikvahethiopia
"...እነሱ ለሚፈፅሙት እያንዳንዱ ድርጊት አፀፋዊ ምላሽ መስጠት ለኛ በጣም ቀላል ነው ፤ ይህንንም እናደርገዋለን" - አቶ አወል አርባ
ትግራይ ክልልን ከአፋር ክልልና አማራ ክልል በሚያዋስኑ አካባቢዎች ስላለው መሬት ላይ ያለ ሁኔት በግልፅ በዝርዝር ባይታወቅም አሁንም ድረስ ወታደራዊ ግጭቶች ስለመኖራቸው የሚገልፁ ጥቆማዎች አሉ።
በአካባቢው ላይ ባለው ግጭት ምክንያት ሺዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተፈናቅለዋል።
የአፋር ክልል ፕሬዜዳንት የሆኑት አቶ አወል አርባ በወቅታዊ የክልሉ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።
አቶ አወል አርባ ፥ በአሁን ሰዓት ህወሓት አጠቃላይ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ዓላማ አንግቦ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል።
"እኛ ኢትዮጵያን ከመራን ኢትዮጵያዊ ነን፤ ኢትዮጵያን ካልመራን ግን ኢትዮጵያዊ አይደለንም ስለዚህ ኢትዮጵያን አፍርሰን እራሳችን መንግስት እንሆናለን የሚል ዓላማ ይዘው የመጡት አሁን ሳይሆን በ1968 ጫካ በነበሩበት ወቅት የፃፉት መፅሃፍ በግልፅ ምስክ እንደሆነና ዶክመቱም በታሪክ ድርሳናት እጅ ይገኛል" ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ አወል ፥ ሽብርተኛ ተብሎ ለተፈረጀው ህወሓት ለሚፈፅመው እያንዳንዱ ድርጊት አፀፋዊ ምላሽ መስጠት እንችላለን ፤ መንገዶችን በህፃናት ለማዘጋት ሞክረዋል፤ እነሱ ላደረጉት ተግባር አፀፋ መስጠት ለኛ ቀላል ነው ይህንንም እናደርገዋለን ብለዋል።
የአፋርን ህዝብ ሰብዓዊነት የጎደለው ትግባርን በመፈፀም አንበረክከዋለሁ ማለት የማታሰብ ነው ያሉት ፕሬዜዳንቱ አፋር በታሪኩ የሽንፈት ታሪክ አጋጥሞት አያውቅም በአሸባሪነት የተፈረጀውን 'ህወሓት' በተባበረ ክንድ እንፋለመዋለን ፤ ዳግም ላይመለስ የሚገባውን ዋጋ በሚገባው ቋንቋ እንሰጠዋለን ሲሉ ዝተዋል ።
ያንብቡ : telegra.ph/Afar-07-24
@tikvahethiopia
#Ethiopia
ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት 4,873 የኮቪድ-19 ላብራቶሪ ምርመራ ያከናወነች ሲሆን 213 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተግኝተዋል፤ ሁለት ሰው ህይወቱ ያለፈ ሲሆን 98 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት 4,873 የኮቪድ-19 ላብራቶሪ ምርመራ ያከናወነች ሲሆን 213 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተግኝተዋል፤ ሁለት ሰው ህይወቱ ያለፈ ሲሆን 98 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
@tikvahethiopia
#Tokyo2020
የ12 ዓመቷ ሶሪያዊ ታዳጊ በቶኪዮ ኦሎምፒክ !
በዘንድሮው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል ሶርያ ትገኝበታለች።
በውድድሩ ላይ በእድሜ ትንሿን ተወዳዳሪ የምታሳትፈው ሶርያ ስትሆን ተወዳዳሪዋ የ12 ዓመቷ ሄንድ ዛዛ ናት ፤ ዛዛ በጠረጴዛ ቴኒስ ነው ሀገሯን ሶሪያ ወክላ በዓለም አቀፉ ውድድር የሚትፋለመው።
የቶኪዮ በእድሜ ትንሿ ተወዳዳሪ ሄንድ ዛዛ በ ኦሎምፒክ የ መጀመሪያ ጨዋታዋ ብትሸነፍም ሌሎች ሕፃናት “ ሕልማቸውን እንዲከተሉ ” ታበረታታለች።
በልጅነቷ በሀገሯ በጦርነት የተጎዳችው ዛዛ ወደ ውድድሩ ለመድረስ “ብዙ የተለያዩ ችግሮችን” ማለፍ እንደነበረባት ተናግራለች።
የቶኪዮ መረጃዎችን ይከታተሉ : @tikvahethsport
የ12 ዓመቷ ሶሪያዊ ታዳጊ በቶኪዮ ኦሎምፒክ !
በዘንድሮው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል ሶርያ ትገኝበታለች።
በውድድሩ ላይ በእድሜ ትንሿን ተወዳዳሪ የምታሳትፈው ሶርያ ስትሆን ተወዳዳሪዋ የ12 ዓመቷ ሄንድ ዛዛ ናት ፤ ዛዛ በጠረጴዛ ቴኒስ ነው ሀገሯን ሶሪያ ወክላ በዓለም አቀፉ ውድድር የሚትፋለመው።
የቶኪዮ በእድሜ ትንሿ ተወዳዳሪ ሄንድ ዛዛ በ ኦሎምፒክ የ መጀመሪያ ጨዋታዋ ብትሸነፍም ሌሎች ሕፃናት “ ሕልማቸውን እንዲከተሉ ” ታበረታታለች።
በልጅነቷ በሀገሯ በጦርነት የተጎዳችው ዛዛ ወደ ውድድሩ ለመድረስ “ብዙ የተለያዩ ችግሮችን” ማለፍ እንደነበረባት ተናግራለች።
የቶኪዮ መረጃዎችን ይከታተሉ : @tikvahethsport