TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ምፅዋ ወደብ⬆️

የኢትዮጵያ የንግድ መርከብ ዛሬ #ምጽዋ ወደብ ላይ መልህቋን ጥላለች፡፡ የንግድ መርከቧ መልህቋን የጣለችው ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ነው ተብሏል፡፡

የንግድ መርከቧ 11 ሺህ ቶን ዚንክ በመጫን ወደ ቻይና እንደምታቀናም ይጠበቃል፡፡ ወደ ምጽዋ ያቀናችው የንግድ መርከብ “መቐለ” ተብላ የምትጠራ መሆኗም ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያና ኤርትራ የሰላምና የወዳጅነት ስምምነት ካደረጉ በኋላ አዲስ የግንኙነት ምእራፍ ውስጥ ገብተዋል፡፡

ከዚህ ቀደምም የሁለቱ ሀገራት የህዝብ ለህዝብ ቡድኖች ወደ አዲስ አበባ እና #አስመራ ማቅናታቸው ይታወሳል፡፡

እንዲሁም በአስመራና በአዲስ አበባ መካከል የንግድ የአየር ትራንስፖርት በይፋ ተጀምሯል፡፡

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia