የኢትዮ-ቴሌኮምን 40 በመቶ ድርሻ ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው አካላት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መግለጽ ይችላሉ ተባለ።
ይህ የተገለፀው ዛሬ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ይርጋና የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ዶክተር ብሩክ ታዬ በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው።
የፍላጎት መግለጫው ከነገ ጀምሮ ለአንድ ወር ክፍት ይሆናል ተብሏል።
ሰነዱን ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው አካላት ከሰኔ 8 ቀን 2013 ጀምሮ ከተቋማቱ ድረ ገጾች ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።
በፍላጎቱ ላይ በመመስረት ከአንድ ወር በኋላ ዓለም አቀፍ ጨረታ ይወጣል ተብሏል።
በቀጣይ የኢትዮ ቴሌኮም 5 በመቶ ድርሻ #ለኢትዮጵውያን እንደሚሸጥ ይፋ ተደርጓል። (ኢዜአ)
@tikvahethiopia
ይህ የተገለፀው ዛሬ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ይርጋና የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ዶክተር ብሩክ ታዬ በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው።
የፍላጎት መግለጫው ከነገ ጀምሮ ለአንድ ወር ክፍት ይሆናል ተብሏል።
ሰነዱን ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው አካላት ከሰኔ 8 ቀን 2013 ጀምሮ ከተቋማቱ ድረ ገጾች ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።
በፍላጎቱ ላይ በመመስረት ከአንድ ወር በኋላ ዓለም አቀፍ ጨረታ ይወጣል ተብሏል።
በቀጣይ የኢትዮ ቴሌኮም 5 በመቶ ድርሻ #ለኢትዮጵውያን እንደሚሸጥ ይፋ ተደርጓል። (ኢዜአ)
@tikvahethiopia