TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ንቁ! #ሰውነት_ከምንም_ይበልጣል!
ሀገር
ብሄር
ዜግነት
ባንዲራ...ሁሉም ነገር እኛ እንደሰው ልጅ ካልተከበርን #አይጠቅሙንም። ሰው ሲገደል፣ ሰው ሲደበደብ፣ ሰው ሲፈናቀል ልባችን #ሊደማ የሚገባው የኛ #ብሄር ተወላጅ ስለሆነ አይደለም እንደኛ ሰው #ብቻ ስለሆነ መሆን አለበት። ያን ጊዜ ለሰማይም ለምድርም መልካም ስራን ሰርተን ማለፍ እንችላለን። ከሁሉም የሚበልጠው ሰውነት ብቻ ነው። ትግሬው የአማራው፤ አማራው የትግሬው ሞት ካላስለቀሰው፣ ኦሮሞው የአማራው፤ አማራው የኦሮሞው ሞት እና ስቃይ ካልተሰማው፣ ኦሮሞው የጋሞው ጋሞውም የኦሮሞው ችግር እና መከራ ካልተሰማው፣ ሲዳማው የወላይታው፤ ወላይታው የሲዳማው ሞት እና ስቃይ ካላስለቀሰው ችግሩ #የፖለቲካ ሳይሆን የሰውነት ስሜት መጥፋት ነው። የሰውነት ስሜት መጥፋት ደግሞ በቁም #መሞት ነው።

መፍትሄው....

እኔም አንተም አንቺም በገባን ልክ ስለሰው ክቡርነት እናስተምር። በየቤታችን ስለሰውነት እንነጋገር። ታች ወርደን ስለሰውነት እናስተምር። ሁላችንም ትልቅ ሀላፊነት አለብን! መጀመሪያ ሰው ሁሉ እንዲከበር፣ እንዲወደድ፣ እንዲፈቀር እንስራ!


ፀጋአብ ወልዴ
#ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia