TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዶክተር ደብረፅዮን‼️

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ለሀገርና ለህዝቦች ሉአላዊነት #መከበር እስከ አሁን ያበረከተው አስተዋጽኦ የሚደነቅ መሆኑን የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ገለጹ፡፡ ዶክተር ደብረጽዮን ሰባተኛው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በዚሁ መግለጫቸው እንዳሉት መከላከያ  ሰራዊቱ ለልማትና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ወሳኝ የሆነውን የህገ-መንግስትና የህዝቦች ሉአላዊነት ያለምንም መሽራረፍ እንዲከበሩ  አርአያነት ያለው ተግባር እያከናወነ ነው፡፡

”በተለይም የሀገራችንና ጎረቤት ሀገራት  ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የሰራቸው ስራዎች ከሀገራዊ ፋይዳው አልፎ በዓለም አቀፍም አርአያነት ያለው ነው” ብለዋል፡፡

በአፍሪካ ሃገራት የተፈጠሩ ግጭቶች ለማረጋጋት በተሰማራበት ሁሉ #በድል_ማጠናቀቁ የህዝባዊነቱ እና የዓላማ ፅናቱ ማሳያ መሆኑን  አስታውቀዋል፡፡

የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት ለሀገርና ለህዝቦች ሉአላዊነት መከበር ፣ ለፍትህና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላበረከተው አስተዋጽኦ #አድናቆታቸውን በመግለጽ አመስግነዋል፡፡

ዶክተር ደብረጽዮን መከላከያ ሰራዊቱ  የሰላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ ወዳድ ህዝቦች አለኝታ እንደሚሆን በመተማመን የትግራይ ህዝብና መንግስት ከጎኑ  እንደሚቆሙ ማረጋገጣቸውን ለክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የሰጡትን መግለጫ ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia