TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
65 ሺህ ብር ወድቆ ያገኘው ወጣት በታማኝነት ለባለቤቱ መለሰ።

በምዕራብ ጎንደር ዞን በቋራ ወረዳ የአይሰጋ ቀበሌ ነዋሪና የጎሚስታ ስራ የሚሰራው ወጣት #ያዩ_ሁነኛው መህሩም ተራራ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ 65 ሺህ ጥሬ ብር ያገኘ ቢሆንም ገንዘቡ ለጠፋበት ለአቶ ሰለሞን ጫቅሌ ምንም ሳይቀንስ 65 ሺህ ብሩን በታማኝነት እንደመለሰለት የቋራ ኮሚኒኬሽን መረጃ ያሳያል።

አቶ ሰለሞን ፥ ገንዘቡን ላገኘለት ወጣት 10 ሺህ ብር ቢሰጠውም ወጣቱ ገንዘቡ አልቀበልም በሚል ሙሉ ታማኝነቱ እና ደግ ስራውን ከፈጣሪው ማግኘት በመፈለጉ ሊቀበለው አለመቻሉን ገልጿል።

ወጣቱ ሰርተን ከምናገኘው ገንዘብ ውጭ የሰው ገንዘብ መጥቶ ሊጠቅመን ይልቅና የራሳችንንም ይዞብን ስለሚጠፋ ሁላችንም የሰው ገንዘብ የሰው ከመሆኑ በዘለለ ለኛ ስለማይጠቅም ሁላችንም ፈጣሪ ሰርተን የምናገኘውን በረከት ያደርግልን ዘንድ ጎን መዋል ይኖርብናል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።

ከሳምንታት በፊት #ጉሌድ_ኢብራሂም_ኡመር የተባለ በጅጅጋ ከተማ በባጃጅ ሹፍርና የተሰማራ ወጣት የትራንስፖርት አገልግሎት የሰጣቸው እናት 300,000 ብር (ሶስት መቶ ሺህ ብር) በባጃጁ ላይ ረስተው ቢወርዱም የብሩ ባለቤት የሆኑትን እናት በመፈለግ የተቀመጡበት ቦታ ድረስ ሄዶ መልሶላቸው ነበር፤ በማህበራዊ ሚዲያም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ለወጣት ጉሌድ ኢብራሂም ኡመር ምስጋና ሲያቀርቡ ነበር።

ለዚህ ተግባሩ የሶማሊ ክልል ፕሬዜደንት አቶ ሙስጠፌ መሀመድም ምስጋና አቅርበውለት እንደነበር አይዘነጋም።

@tikvahethiopia