TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ ገብቷል! "ለአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፤ በተደረገው ምርመራ አንድ (1) ጃፓናዊ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። ሁላችንም ከእጅ ንክኪዎች እና አላስፈላጊ ስብሰባዎች እንቆጠብ ለማለት እፈልጋለሁ።" - ኢንጂነር ታከለ ኡማ @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኮቪድ-19 ኢትዮጵያ ከገባ 1 ዓመት ሞላው።

ልክ በዚህ ሰዓት ነው የዛሬ ዓመት ኮሮና ቫይረስ ኢትዮጵያ እንደገባ በይፋዊ መግለጫ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተነገረው።

መጀመሪያ ግን በወቅቱ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ ናቸው በፌስቡክ ገፃቸው ፥ "...አንድ (1) ጃፓናዊ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። ሁላችንም ከእጅ ንክኪዎች እና አላስፈላጊ ስብሰባዎች እንቆጠብ" ሲሉ መልዕክት ያሰራጩት።

በኃላም ዶ/ር ሊያ እና ዶ/ር ኤባ በቴሌቪዥን ወጥተው ኮቪድ-19 የተያዘ የመጀመሪያው ሰው እንደተገኘ ፤ ስለግለሰቡ ዝርዝር መረጃ ለህዝብ ይፋ አደረጉ።

ብዙዎችም በሰሙት ነገር እጅግ ተሸበሩ፤ ተጨነቁ።

በወቅቱ የነበረ ሁኔታ በጥቂቱ ፦

- ኢ/ር ታከለ ቀድመው ማሳወቃቸው t.iss.one/tikvahethiopia/47204
- የእነ ዶ/ር ሊያ መግለጫ t.iss.one/tikvahethiopia/47206
- ማስክ እና ሳኒታዘር ለመግዛት የነበረው ሰልፍ t.iss.one/tikvahethiopia/47215
- የሳኒታዘር እና ማስክ ዋጋ መጨመር ነዋሪዎችን አማሮ ነበር t.iss.one/tikvahethiopia/47226
- የወቅቱን ሁኔታ ተጠቅመው ዋጋ የጨመሩ ነጋዴዎች t.iss.one/tikvahethiopia/47231
- የዶ/ር ቴድሮስ (WHO) #TheSafeHandsChallenge t.iss.one/tikvahethiopia/47241
- በወቅቱ የነበረው የትግራይ ክልል መንግስት በአስቸኳይ ነፃ የጥሪ ማዕከል ማዘጋጀቱ t.iss.one/tikvahethiopia/47243
- በወቅቱ እጅግ መነጋገሪያ ከነበረው ጉዳይ በኮቪድ-19 ተጠርጥሮ ሲወሰድ አምቡላስ ሰብሮ ያመለጠው ሰው t.iss.one/tikvahethiopia/47307
- ከ3 ቀን በኃላ በሰበር ዜና መንግስት ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ የሚሉና ሌሎች ውሳኔዎች ማሳለፉ t.iss.one/tikvahethiopia/47372
- ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ የዶ/ር ቴድሮስን ጥሪ ተቀብለው የንፁህ እጆች ዘመቻን መካፈላቸው t.iss.one/tikvahethiopia/47386
- አሁን በእስር ላይ የሚገኙት የመንግስት ዋነኛ ተቃዋሚ መሪው አቶ ጃዋር እና ሎሎችም፣ ጋዜጠኞች የንፁህ እጆችን ዘመቻ መቀላቀላቸው t.iss.one/tikvahethiopia/47387
- በመከላከያ ሰራዊት አዲስ ምልመላ ፣ ፍቃድ፣ በሰራዊት ካምፕ እና መኖሪያ ቤት ግንኙነት መገታቱ t.iss.one/tikvahethiopia/47505
- እርዳት ማሰባሰቡ፣ መተባበሩ ፣ መተጋገዙ t.iss.one/tikvahethiopia/47686
- በየቦታው ርቀት እንዲጠበቅ ፣ ሰዎች እጅ እንዲታጠቡ ዘመቻ መደረጉ።

ብዙ ብዙ...

በወቅቱ ሁሉም ሰው ፣ ሚዲያው ወሬው ሁሉ ስለ ኮቪድ-19 ነበር። በእጅጉ ጥንቃቄ እንዲደረግም ይቀሰቀስ ነበር። የሰዎች ጭንቀት ፍርሃትም አይሎ ነበር።

ዛሬስ ?

ዛሬ ግን በሀገራችን ወረርሽኙ አስከፊ ደረጃ ላይ ሲደርስ መዘናጋቱ ጨምሯል ፤ በየዕለቱ የሰዎች ህይወት ያለፋል ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቫይረሱ ይያዛሉ ፣ የፅኑ ህሙማን ቁጥር ከአቅም በላይ ሆኗል፣ ከመንግስት ኃላፊዎች ጀምሮ ጉዳዩ ተዘንግቷል ፣ መንግስት ብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሰልፍ ሲያደርጉ ያበረታታል ፣ በሚያዲያም ቅስቀሳ ይደረጋል ፤ አርአያ የሚሆንም ሰው ቀንሷል።

ዛሬም የጤና ባለሞያዎች ደከመን ሰለቸን ሳይሉ ወረርሽኙን እየተጋፈጡ ነው (እናመሰግናለን) !

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia