የጥምቀት በዓል በኤርትራ ተከበረ።
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመግታት በተቀመጠው ጥብቅ በሆነ ገደብ የዘንድሮው የጥምቀት በዓል #በኤርትራ ተከብሯል።
በበዓሉ በኮቪድ-19 ምክንያት በርካቶች መገኘት አልቻሉም።
በኤርትራ መዲና "አስመራ ከተማ" (ከላይ ፎቶው ተያይዟል) በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች የጥምቀት በዓል በልዩ ሁኔታ ተከብሯል።
ኤርትራ ውስጥ እስካሁን በኮቪድ-19 መያዛቸው የተረጋገጠ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር 1,877 ሲሆን ከነዚህ መካከል 1,073 ሰዎች አገግመዋል ፤ 6 ሰዎች ደግሞ በበሽታው ሞተዋል።
ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ በሀገሪቱ ጥብቅ የሆነ ቁጥጥር እየተደረገ ይገኛል።
Photo : Yemane G. Meskel
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመግታት በተቀመጠው ጥብቅ በሆነ ገደብ የዘንድሮው የጥምቀት በዓል #በኤርትራ ተከብሯል።
በበዓሉ በኮቪድ-19 ምክንያት በርካቶች መገኘት አልቻሉም።
በኤርትራ መዲና "አስመራ ከተማ" (ከላይ ፎቶው ተያይዟል) በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች የጥምቀት በዓል በልዩ ሁኔታ ተከብሯል።
ኤርትራ ውስጥ እስካሁን በኮቪድ-19 መያዛቸው የተረጋገጠ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር 1,877 ሲሆን ከነዚህ መካከል 1,073 ሰዎች አገግመዋል ፤ 6 ሰዎች ደግሞ በበሽታው ሞተዋል።
ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ በሀገሪቱ ጥብቅ የሆነ ቁጥጥር እየተደረገ ይገኛል።
Photo : Yemane G. Meskel
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በጃንሜዳ ያደሩ ታቦታት ወደ መቅደሳቸው እየተሸኙ ነው።
አ/አ ጃንሜዳ ካደሩት የ15 ደብሮች ታቦታት መካከል የ12 ደብሮች ታቦታት ወደ መቅደሳቸው እየተሸኙ ነው።
ምዕመናኑ ታቦታቱን በእልልታና በሆታ፤ ካህናቱ በአኮቴት (ምስጋና) እና ሽብሸባ ታቦታቱን ወደ መቅደሳቸው እየሸኙ ይገኛሉ። ~ ENA
@tikvahethiopia
አ/አ ጃንሜዳ ካደሩት የ15 ደብሮች ታቦታት መካከል የ12 ደብሮች ታቦታት ወደ መቅደሳቸው እየተሸኙ ነው።
ምዕመናኑ ታቦታቱን በእልልታና በሆታ፤ ካህናቱ በአኮቴት (ምስጋና) እና ሽብሸባ ታቦታቱን ወደ መቅደሳቸው እየሸኙ ይገኛሉ። ~ ENA
@tikvahethiopia
የጥምቀት በዓል በካቶሊክ እምነት ተከታዮች ዘንድ ተከበረ።
የጥምቀት በዓል በካቶሊክ እምነት ተከታዮች ዘንድ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ዝግጅቶች ተከብሯል።
PHOTO : ኢቲቪ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የጥምቀት በዓል በካቶሊክ እምነት ተከታዮች ዘንድ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ዝግጅቶች ተከብሯል።
PHOTO : ኢቲቪ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ጥምቀት በዮርዳኖስ ወንዝ ተከበረ።
በዛሬው ዕለት በእስራኤል (እየሩሳሌም) የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ገዳማት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንባቆም እንዲሁም የገዳሙ መነኮሳት እየሱስ ክርስቶስ በተጠመቀበት ቦታ "ዮርዳኖስ ወንዝ" ወርደው በዓሉን አክብረዋል።
በዮርዳኖስ ወንዝ የሚከበረው በዓል ለሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ተራ የተሰጠ ሲሆን ፣ ዛሬ የግሪክ ኦርቶዶክስ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ነገ የሶሪያና የግብጽ፣ በቀጣይ የአርመን፣ የሩሲያ እና ሌሎችም ያከብራሉ።
የዘንድሮው በዓል የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል በወጣው መመሪያ መሠረት የእንቅስቃሴ ገደብ ስለተጣለ ለመግባት የተፈቀደው ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ በመሆኑ ብዙ ምዕመናን መሄድ አልቻሉም።
Via Ethiopian Embassy in Israel (AMMA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በዛሬው ዕለት በእስራኤል (እየሩሳሌም) የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ገዳማት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንባቆም እንዲሁም የገዳሙ መነኮሳት እየሱስ ክርስቶስ በተጠመቀበት ቦታ "ዮርዳኖስ ወንዝ" ወርደው በዓሉን አክብረዋል።
በዮርዳኖስ ወንዝ የሚከበረው በዓል ለሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ተራ የተሰጠ ሲሆን ፣ ዛሬ የግሪክ ኦርቶዶክስ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ነገ የሶሪያና የግብጽ፣ በቀጣይ የአርመን፣ የሩሲያ እና ሌሎችም ያከብራሉ።
የዘንድሮው በዓል የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል በወጣው መመሪያ መሠረት የእንቅስቃሴ ገደብ ስለተጣለ ለመግባት የተፈቀደው ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ በመሆኑ ብዙ ምዕመናን መሄድ አልቻሉም።
Via Ethiopian Embassy in Israel (AMMA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በከተራ በዓል ላይ በደረሱ የኤሌክሪክ አደጋዎች 2 ወጣቶች ሞቱ።
ትላንት በአማራ ክልል በሰቆጣ እና በኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞን ሸረሮ ከተሞች የከተራ በዓል በሚከበርበት ወቅት በደረሰ የኤሌክትሪክ አደጋ የ2 ወጣቶች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አሰታውቋል።
የሰቆጣ ከተማ ፖሊስ ፅህፈት ቤት በከተማው የከተራ በዓል በሚከበርበት ወቅት ታቦታቱን ከፀሃይ የሚከላከል ጥላ ከኤሌክትሪክ ጋር በመነካካቱ በተከሰተ የኤሌክትሪክ አደጋ የአንድ ወጣት ህይወት ወድያው አልፏል።
በሌሎች ጥላውን በመግፈፍ ላይ በነበሩ ስምንት ወጣቶች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወጣቶች በሰቆጣ ተፈራ ሃይሉ መታሰቢያ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረሊባኖስ ወረዳ ሸረሮ ከተማ ለጥምቀት በዓል ማድመቂያ ሰንደቅ ዓላማ ለመስቀል የሞከረ የ24 ዓመት ወጣት ህይወቱ ማለፉን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል።
ወጣቱ ፎቅ ላይ ሆኖ የወረወረው ገመድ 33 ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ኅይል ማስተላለፊያ ገመድ ላይ በማረፉ በእርጥብ እንጨት ለማንሳት ሲሞክር በኤሌክትሪክ ሀይል ተገፍተሮ ሊወድቅ ችሏል።
ወጣቱ ወደ ሽረሮ ጤና ጣቢያ ቢወሰድም ከ30 ደቂቃ በኃላ ህይወቱ አልፏል። ~ ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ትላንት በአማራ ክልል በሰቆጣ እና በኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞን ሸረሮ ከተሞች የከተራ በዓል በሚከበርበት ወቅት በደረሰ የኤሌክትሪክ አደጋ የ2 ወጣቶች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አሰታውቋል።
የሰቆጣ ከተማ ፖሊስ ፅህፈት ቤት በከተማው የከተራ በዓል በሚከበርበት ወቅት ታቦታቱን ከፀሃይ የሚከላከል ጥላ ከኤሌክትሪክ ጋር በመነካካቱ በተከሰተ የኤሌክትሪክ አደጋ የአንድ ወጣት ህይወት ወድያው አልፏል።
በሌሎች ጥላውን በመግፈፍ ላይ በነበሩ ስምንት ወጣቶች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወጣቶች በሰቆጣ ተፈራ ሃይሉ መታሰቢያ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረሊባኖስ ወረዳ ሸረሮ ከተማ ለጥምቀት በዓል ማድመቂያ ሰንደቅ ዓላማ ለመስቀል የሞከረ የ24 ዓመት ወጣት ህይወቱ ማለፉን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል።
ወጣቱ ፎቅ ላይ ሆኖ የወረወረው ገመድ 33 ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ኅይል ማስተላለፊያ ገመድ ላይ በማረፉ በእርጥብ እንጨት ለማንሳት ሲሞክር በኤሌክትሪክ ሀይል ተገፍተሮ ሊወድቅ ችሏል።
ወጣቱ ወደ ሽረሮ ጤና ጣቢያ ቢወሰድም ከ30 ደቂቃ በኃላ ህይወቱ አልፏል። ~ ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#AddisAbabaPoliceCommission
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የከተራ እና የጥምቀት በዓል በሠላም መጠናቀቁን አስታውቋል፤ ህብረተሰቡ ለበዓሉ በሠላም መጠናቀቅ ላበረከተው አስተዋፅኦ ኮሚሽኑ ምስጋና አቅርቧል፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የከተራ እና የጥምቀት በዓል በሠላም መጠናቀቁን አስታውቋል፤ ህብረተሰቡ ለበዓሉ በሠላም መጠናቀቅ ላበረከተው አስተዋፅኦ ኮሚሽኑ ምስጋና አቅርቧል፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ጃንሜዳ በከተራ እና በጥምቀት በዓላት ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለው ክስ እንደተመሰረተባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
በከተራና በበዓሉ ዕለት በነበረው የፀበል መርጨት ስነ ስርዓት ወቅት የነበረውን ግፊያ እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም 5 የስርቆት እና 1 የቅሚያ ወንጀል ተፈፅሟል፡፡
እንዲሁም አንድ ግለሰብ አደንዛዥ ዕፅ ይዞ ሲንቀሳቀስ በፍተሻ ተገኝቶበታል፡፡
በአጠቃላይ ወንጀሎቹን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 7 ግለሰቦች ተይዘው ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን 5 የተሰረቁ ሞባይል ስልኮችም በተጠርጣሪዎቹ እጅ መገኘታቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡
በበዓላቱ ወቅት ሊፈፀሙ የሚችሉ ወንጀሎችን አስቀድሞ ከመከላከል ባሻገር ተፈፅመው ሲገኙ ምርመራ በማጣራት አገልግሎት ለመስጠት በጃን ሜዳ ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያ በመክፈት እና የምርመራ ቡድን ተደራጅቶ ከዐቃቤ ህግ ጋር መሰራቱን ኮሚሽኑ ገልጿል።
Via Addis Ababa Police Commission
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በአዲስ አበባ ጃንሜዳ በከተራ እና በጥምቀት በዓላት ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለው ክስ እንደተመሰረተባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
በከተራና በበዓሉ ዕለት በነበረው የፀበል መርጨት ስነ ስርዓት ወቅት የነበረውን ግፊያ እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም 5 የስርቆት እና 1 የቅሚያ ወንጀል ተፈፅሟል፡፡
እንዲሁም አንድ ግለሰብ አደንዛዥ ዕፅ ይዞ ሲንቀሳቀስ በፍተሻ ተገኝቶበታል፡፡
በአጠቃላይ ወንጀሎቹን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 7 ግለሰቦች ተይዘው ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን 5 የተሰረቁ ሞባይል ስልኮችም በተጠርጣሪዎቹ እጅ መገኘታቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡
በበዓላቱ ወቅት ሊፈፀሙ የሚችሉ ወንጀሎችን አስቀድሞ ከመከላከል ባሻገር ተፈፅመው ሲገኙ ምርመራ በማጣራት አገልግሎት ለመስጠት በጃን ሜዳ ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያ በመክፈት እና የምርመራ ቡድን ተደራጅቶ ከዐቃቤ ህግ ጋር መሰራቱን ኮሚሽኑ ገልጿል።
Via Addis Ababa Police Commission
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በሁመራ፣_በዳንሻ_እና_በቢሶበር_ሲቪል_ሰዎች_ስለሚገኙበት_ሁኔታ_የተደረገ_አጭር_የክትትል_ሪፖርት_2.pdf
199 KB
ትግራይ እና አማራ ክልል ፡ የሲቪል ሰዎች ደኅንነትና ከትግራይ ክልል የተፈናቀሉ ሰዎች ሁኔታ ወደ ሰብአዊ ቀውስ ሊያመራ ይችላል።
አስቸኳይ ሰብአዊ እርዳታ እና ድጋፍ ሊቀርብ ይገባል። - ኢሰመኮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አስቸኳይ ሰብአዊ እርዳታ እና ድጋፍ ሊቀርብ ይገባል። - ኢሰመኮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"..ያለው ችግር ከሚነገረው በላይ ነው" - የትግራይ ቲክቫህ አባላት
በትግራይ ክልል ባለው የኔትዎርክ መቋረጥ አሁንም ድረስ በርካታ የትግራይ የቲክቫህ አባላትን ማግኘት አልተቻለም።
ነገር ግን የተለያዩ የትራንስፖርት አመራጮችን ተጠቅመው ወደ መቐለ የገቡ አባላት በርካታ ጉዳዮችን በስልክ እያሳወቁ ይገኛሉ።
በጦርነቱ ወቅት ያለፉትን ግዚያት በሚመለከት ወደፊት ለቲክቫህ አባላት በይፋ እንደሚያሳውቁ ገልፀው አሁን ላይ በትግራይ ስላለው መጠነ ሰፊ ችግር ማሳወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በተለይ ደግሞ ከከተሞች ወጣ ባሉና ጦርነቱ ከፍተኛ በነበረባቸው ቦታዎች ያሉ ሰዎች ዛሬም ድረስ በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሆኑ አሳውቀዋል።
ያለው ችግር ከሚነገረው በላይ ነው የሚሉት የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ችግሩ በመንግስት ብቻ ይፈታል ብለው እንደማያስቡ አስገንዝበዋል።
ከዚህ ቀደም ሰርተው ግቢ የሚያገኙ፣ የሚበሉ በጦርነቱ ምክንያት የከፋ ችግር ውስጥ ወድቀዋል።
አሁንም የደህንነት ችግር ያለባቸው ቦታዎች እንዳሉ ጠቁመው ፣ ባለፉት ወራት ኤሌክትሪክ ኃይል ባለመኖሩ ፣ ምግብ ማግኘትም አስቸጋሪ በመሆኑ፣ ባንክ ባለመኖሪ፣ ስራ ለመስራት ባለመቻሉ በርካቶችም ለረሃብ አጋልጧቸዋል ብለዋል።
"ጦርነት እጅግ አስከፊ ነገር ነው ፤ በጦርነት ወቅት ስለምን ማሰብ እንዳለብህ እንኳን አታውቀም ሁሉም ነገር ቀጥ ብሎ ይቆማል ፤ በዚህ መሀል በተለይ ህፃናት፣ ተማሪዎች፣ ሴቶች ፣ እናቶች፣ እጅጉን ይጎሳቆላሉ ከነዚህ አካላት ጋር አብሮ መቆም ያስፈልጋል" ሲሉ ተናግረዋል።
ተጨማሪ :https://telegra.ph/TikvahEthiopia-01-19
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ባለው የኔትዎርክ መቋረጥ አሁንም ድረስ በርካታ የትግራይ የቲክቫህ አባላትን ማግኘት አልተቻለም።
ነገር ግን የተለያዩ የትራንስፖርት አመራጮችን ተጠቅመው ወደ መቐለ የገቡ አባላት በርካታ ጉዳዮችን በስልክ እያሳወቁ ይገኛሉ።
በጦርነቱ ወቅት ያለፉትን ግዚያት በሚመለከት ወደፊት ለቲክቫህ አባላት በይፋ እንደሚያሳውቁ ገልፀው አሁን ላይ በትግራይ ስላለው መጠነ ሰፊ ችግር ማሳወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በተለይ ደግሞ ከከተሞች ወጣ ባሉና ጦርነቱ ከፍተኛ በነበረባቸው ቦታዎች ያሉ ሰዎች ዛሬም ድረስ በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሆኑ አሳውቀዋል።
ያለው ችግር ከሚነገረው በላይ ነው የሚሉት የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ችግሩ በመንግስት ብቻ ይፈታል ብለው እንደማያስቡ አስገንዝበዋል።
ከዚህ ቀደም ሰርተው ግቢ የሚያገኙ፣ የሚበሉ በጦርነቱ ምክንያት የከፋ ችግር ውስጥ ወድቀዋል።
አሁንም የደህንነት ችግር ያለባቸው ቦታዎች እንዳሉ ጠቁመው ፣ ባለፉት ወራት ኤሌክትሪክ ኃይል ባለመኖሩ ፣ ምግብ ማግኘትም አስቸጋሪ በመሆኑ፣ ባንክ ባለመኖሪ፣ ስራ ለመስራት ባለመቻሉ በርካቶችም ለረሃብ አጋልጧቸዋል ብለዋል።
"ጦርነት እጅግ አስከፊ ነገር ነው ፤ በጦርነት ወቅት ስለምን ማሰብ እንዳለብህ እንኳን አታውቀም ሁሉም ነገር ቀጥ ብሎ ይቆማል ፤ በዚህ መሀል በተለይ ህፃናት፣ ተማሪዎች፣ ሴቶች ፣ እናቶች፣ እጅጉን ይጎሳቆላሉ ከነዚህ አካላት ጋር አብሮ መቆም ያስፈልጋል" ሲሉ ተናግረዋል።
ተጨማሪ :https://telegra.ph/TikvahEthiopia-01-19
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"...ለሶስት ወራት በከፍተኛ ችግር ውስጥ ነን" - በትግራይ ክልል መንግስት ሰራተኞች
(በጀርመን ሬድዮ)
በትግራይ ክልል ማይጨውና አካባቢው የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ደምወዛቸው ለ3 ወራትያ ህል ባለመከፈሉ ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር መዳረጋቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።
አንድ የማይጨው ከተማ ነዋሪ፥ "ምንም እንኳ ባንኮች ለአገልግሎት ክፍት ቢሆኑም ፣ ትራንስፖርት አገልግሎት ቢቀጥልም ሆነ ኤሌክትሪክ ሥራ ቢጀምሩም ደመወዝ ከኅዳር 2013 ዓ.ም ጀምሮ አልወሰድም፤ በከፍተኛ ችግር ላይ ነን" ሲሉ ተናግረዋል።
መንግሥት ደመወዝ ባለመክፈሉ ምክንያት የእለት እርዳታም ለማግኘት የመንግሥት ሠራተኛ ናችሁ በመባላቸው ብዙዎቹ ለችግር ተጋልጠዋል።
አንድ መምህር ዳግሞ እስካሁን ኑሯቸውን የሚገፉት ከእነርሱ የተሸለ ገቢ ካላቸው ወገኖች በሚያገኙት ድጋፍ መሆኑን ገልፀው መንግሥት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ፥ በነበረው ችግር ምክንያት ባንኮች አገልግሎት ሳይሰጡ መቆየታቸውን አስታውሰው አሁን ላይ የተሸለ ነገር ስለተፈጠረ ለሠራተኞቹ በቅርቡ ደመወዛቸው ይከፈላል ብለዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(በጀርመን ሬድዮ)
በትግራይ ክልል ማይጨውና አካባቢው የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ደምወዛቸው ለ3 ወራትያ ህል ባለመከፈሉ ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር መዳረጋቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።
አንድ የማይጨው ከተማ ነዋሪ፥ "ምንም እንኳ ባንኮች ለአገልግሎት ክፍት ቢሆኑም ፣ ትራንስፖርት አገልግሎት ቢቀጥልም ሆነ ኤሌክትሪክ ሥራ ቢጀምሩም ደመወዝ ከኅዳር 2013 ዓ.ም ጀምሮ አልወሰድም፤ በከፍተኛ ችግር ላይ ነን" ሲሉ ተናግረዋል።
መንግሥት ደመወዝ ባለመክፈሉ ምክንያት የእለት እርዳታም ለማግኘት የመንግሥት ሠራተኛ ናችሁ በመባላቸው ብዙዎቹ ለችግር ተጋልጠዋል።
አንድ መምህር ዳግሞ እስካሁን ኑሯቸውን የሚገፉት ከእነርሱ የተሸለ ገቢ ካላቸው ወገኖች በሚያገኙት ድጋፍ መሆኑን ገልፀው መንግሥት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ፥ በነበረው ችግር ምክንያት ባንኮች አገልግሎት ሳይሰጡ መቆየታቸውን አስታውሰው አሁን ላይ የተሸለ ነገር ስለተፈጠረ ለሠራተኞቹ በቅርቡ ደመወዛቸው ይከፈላል ብለዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"...ወታደሮቼ በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት አልተሳተፉም" - ሶማሊያ
የሶማሊያ መንግሥት ወታደሮቹ በሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ተሳትፈዋል ሲሉ የወጡ ዘገባዎች ትክክል አይደሉም አለ።
ይህን ያለው የቀድሞ የሶማሊያ ከፍተኛ የደኅንነት ባለስልጣን ከጥቂት ወራት በፊት ኤርትራ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሶማሊያ ወታደሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ተገድለዋል ካሉ በኋላ ነው።
አብዲሰላም ጉሌድ የተባሉት የሶማሊያ ብሔራዊ የደኅንነትና መረጃ ተቋም የቀድሞ ምክትል ኃላፊ ተጨባጭ #ማስረጃ ሳያቀርቡ ለአንድ የግል ሬዲዮ "400 የሚደርሱ የሶማሊያ ወታደሮች" በትግራይ ክልል በተካሄደው ውጊያ ተገድለዋል ሲሉ ተናግረዋል።
የቀድሞው ባለስልጣን ከኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ጋር ተሰልፈው ሲዋጉ ተገድለዋል ያሏቸው የሶማሊያ ወታደሮች በ20 እና በ30 ዓመት ዕድሜ ውስጥ የነበሩ ናቸው።
ይህ የግለሰቡ ንግግር በተለያዩ የሶማሊያ ክፍሎች ውስጥ ቁጣን ቀስቅሷል።
ልጆቻቸው ለወታደራዊ ስልጠና ወደ ውጪ አገራት የሄዱ ቤተሰቦች ጉዳዩ እንዳሳሰባቸው በመግለጽ መንግሥት ልጆቻቸው የት እንዳሉ እና በሕይወት ይኑሩ ወይም ይሙቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
የሶማሊያው የማስታወቂያ ሚኒስትር ኦስማን አቡከር ዱቤ ፥ "የሶማሊያ ኃይሎች በቅርቡ በኢትዮጵያ በተካሄደው ውጊያ ላይ አልተሳተፉም" ብለዋል።
ሚኒስትሩ ከቢቢሲ የሶማሊኛ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልልስ "ከዚህ ቀደም የሶማሊያ ወታደሮች በሊቢያና በአዘርባጃን ውስጥ በተካሄዱ ውጊያዎች ውስጥ ተሳትፈዋል ተብሎ ቢወራም ኋላ ወሬው ሐሰተኛ መሆኑ ተረጋግጧል" ብለዋል።
ጨምረው የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ግጭት ውስጥ ተሳትፈዋል የተባለው ወሬ ሐሰተኛ ነው ብለዋል። ~ ቢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሶማሊያ መንግሥት ወታደሮቹ በሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ተሳትፈዋል ሲሉ የወጡ ዘገባዎች ትክክል አይደሉም አለ።
ይህን ያለው የቀድሞ የሶማሊያ ከፍተኛ የደኅንነት ባለስልጣን ከጥቂት ወራት በፊት ኤርትራ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሶማሊያ ወታደሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ተገድለዋል ካሉ በኋላ ነው።
አብዲሰላም ጉሌድ የተባሉት የሶማሊያ ብሔራዊ የደኅንነትና መረጃ ተቋም የቀድሞ ምክትል ኃላፊ ተጨባጭ #ማስረጃ ሳያቀርቡ ለአንድ የግል ሬዲዮ "400 የሚደርሱ የሶማሊያ ወታደሮች" በትግራይ ክልል በተካሄደው ውጊያ ተገድለዋል ሲሉ ተናግረዋል።
የቀድሞው ባለስልጣን ከኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ጋር ተሰልፈው ሲዋጉ ተገድለዋል ያሏቸው የሶማሊያ ወታደሮች በ20 እና በ30 ዓመት ዕድሜ ውስጥ የነበሩ ናቸው።
ይህ የግለሰቡ ንግግር በተለያዩ የሶማሊያ ክፍሎች ውስጥ ቁጣን ቀስቅሷል።
ልጆቻቸው ለወታደራዊ ስልጠና ወደ ውጪ አገራት የሄዱ ቤተሰቦች ጉዳዩ እንዳሳሰባቸው በመግለጽ መንግሥት ልጆቻቸው የት እንዳሉ እና በሕይወት ይኑሩ ወይም ይሙቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
የሶማሊያው የማስታወቂያ ሚኒስትር ኦስማን አቡከር ዱቤ ፥ "የሶማሊያ ኃይሎች በቅርቡ በኢትዮጵያ በተካሄደው ውጊያ ላይ አልተሳተፉም" ብለዋል።
ሚኒስትሩ ከቢቢሲ የሶማሊኛ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልልስ "ከዚህ ቀደም የሶማሊያ ወታደሮች በሊቢያና በአዘርባጃን ውስጥ በተካሄዱ ውጊያዎች ውስጥ ተሳትፈዋል ተብሎ ቢወራም ኋላ ወሬው ሐሰተኛ መሆኑ ተረጋግጧል" ብለዋል።
ጨምረው የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ግጭት ውስጥ ተሳትፈዋል የተባለው ወሬ ሐሰተኛ ነው ብለዋል። ~ ቢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#KonsoZone
ኮንሶ ዞን ካራት ከተማ በዛሬው ዕለት የተከበረው የጥምቀት በዓል እንዲሁም ትላንት የተከበረው የከተራ በዓል ያለአንዳች የፀጥታ ችግር በሠላም ተከብሮ መጠናቀቁ ተገልጾልናል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ኮንሶ ዞን ካራት ከተማ በዛሬው ዕለት የተከበረው የጥምቀት በዓል እንዲሁም ትላንት የተከበረው የከተራ በዓል ያለአንዳች የፀጥታ ችግር በሠላም ተከብሮ መጠናቀቁ ተገልጾልናል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Tigray
"...የዕለት ደራሽ እርዳታው በተገቢው መንገድ እየደረሰን አይደለም" - በመቐለ የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖች
ባለፉት 2 ወራት በትግራይ በተካሄደው ጦርነት የትግራይ ምዕራባዊ ዞን ነዋሪዎች ከሌላው አካባቢ በተለየ ሁኔታ ወደሌላው የትግራይ አካባቢ እና ወደ ሱዳን ተፈናቅለዋል።
ተፈናቃይ ወገኖች በጦርነቱ ምክንያት ለከባድ ሰብዓዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተዳርገዋል።
የተለያዩ ቤተሰቦቻቸው ወደ ተለያየ ቦታ በመበታተናቸው ህልውናቸውን ለማረጋገጥ እና ወደ ቤታቸው ለመመለስ የተመቻቸ ነገር እንደሌለ በመቐለ የተጠሉሉ ዜጎች ለትግራይ ቲቪ ተናግረዋል።
ከተፈናቃዮች መካከል አንደኛው ከወላጅ እናቱ እና ከእህቱ ጋር ይኖር እንደነበር እና ሁሉም ህይወቱን ለማትረፍ ወደ ተለያየ ቦታ እንደሸሸ ገልፆ በዚህም ምክንያት እናትና እህቱ የት እንደገቡ ፤ ይኑሩ ይሙቱ እንደማያውቅ እነሱም ስለሱ የሚያወቁት ነገር እንደሌለ ተናግሯል።
ሌላኛው ከሁመራ የተፈናቀለ ግለሰብ፥ ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይሁን ሌላ አካል ያደረገው ነገርና ስለመመለሳቸውም የተሰጣቸው መረጃ እንደሌለ ገልጿል።
ተፈናቃዩ ፥ ቤቶቻቸውን ሌሎች ሰዎች እንደገቡባቸውና ብዙ ንብረት ትተው በመፈናቀላቸው ከባድ ችግር ውስጥ እንዳሉ ገልጿል።
አንድ እድሜያቸው ገፋ ያለ እናት ደግሞ : "የራሴ ቤት እና እርሻ ነበረኝ፥ ልጄ እዛው ነው በስልክ እንደነገረኝ ከሆነ ንብረታችን በሙሉ እየተወሰደ ነው። ለኔ ግን እንኳን ልጄ አልሞተ እንጂ ንብረት ቀረብኝ አልልም ሰርቼ መልሰዋለሁ።" ብለዋል።
የፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የዕለት ደራሽ እርዳታ እየሰጠ ቢሆንም ተፈናቃዮች ተገቢውን እና በቂ ድጋፍ እያገኙ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
"...የዕለት ደራሽ እርዳታው በተገቢው መንገድ እየደረሰን አይደለም" - በመቐለ የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖች
ባለፉት 2 ወራት በትግራይ በተካሄደው ጦርነት የትግራይ ምዕራባዊ ዞን ነዋሪዎች ከሌላው አካባቢ በተለየ ሁኔታ ወደሌላው የትግራይ አካባቢ እና ወደ ሱዳን ተፈናቅለዋል።
ተፈናቃይ ወገኖች በጦርነቱ ምክንያት ለከባድ ሰብዓዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተዳርገዋል።
የተለያዩ ቤተሰቦቻቸው ወደ ተለያየ ቦታ በመበታተናቸው ህልውናቸውን ለማረጋገጥ እና ወደ ቤታቸው ለመመለስ የተመቻቸ ነገር እንደሌለ በመቐለ የተጠሉሉ ዜጎች ለትግራይ ቲቪ ተናግረዋል።
ከተፈናቃዮች መካከል አንደኛው ከወላጅ እናቱ እና ከእህቱ ጋር ይኖር እንደነበር እና ሁሉም ህይወቱን ለማትረፍ ወደ ተለያየ ቦታ እንደሸሸ ገልፆ በዚህም ምክንያት እናትና እህቱ የት እንደገቡ ፤ ይኑሩ ይሙቱ እንደማያውቅ እነሱም ስለሱ የሚያወቁት ነገር እንደሌለ ተናግሯል።
ሌላኛው ከሁመራ የተፈናቀለ ግለሰብ፥ ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይሁን ሌላ አካል ያደረገው ነገርና ስለመመለሳቸውም የተሰጣቸው መረጃ እንደሌለ ገልጿል።
ተፈናቃዩ ፥ ቤቶቻቸውን ሌሎች ሰዎች እንደገቡባቸውና ብዙ ንብረት ትተው በመፈናቀላቸው ከባድ ችግር ውስጥ እንዳሉ ገልጿል።
አንድ እድሜያቸው ገፋ ያለ እናት ደግሞ : "የራሴ ቤት እና እርሻ ነበረኝ፥ ልጄ እዛው ነው በስልክ እንደነገረኝ ከሆነ ንብረታችን በሙሉ እየተወሰደ ነው። ለኔ ግን እንኳን ልጄ አልሞተ እንጂ ንብረት ቀረብኝ አልልም ሰርቼ መልሰዋለሁ።" ብለዋል።
የፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የዕለት ደራሽ እርዳታ እየሰጠ ቢሆንም ተፈናቃዮች ተገቢውን እና በቂ ድጋፍ እያገኙ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT