TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NetBlocks

ዛሬ ምርጫ በምታካሂደው ኡጋንዳ ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ ተቋረጠ።

ኢተርኔት የተቋረጠው ከትላንት ጀምሮ ነው።

ብሎክስ በትዊተር ገፁ ፥ ከትናንትና ምሽት 1 ሰዓት ጀምሮ በመላው አገሪቱ ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል ብሏል።

ይህ የባለስልጣናቱ ኢንተርኔት የማቋረጥ ውሳኔ በቅርቡ የትኛውም የትኛውም አይነት ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲዘጉ የተላለፈውንም ይከተላል።

ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኑ እንዳሉት ፌስቡክ የፓርቲያቸውን ደጋፊዎች አካውንት እንዲታገድ በማድረጉ ይህ ውሳኔ እንደተላለፈ አስታውቀዋል።

በአፍሪካ ውስጥ ለረዥም ዘመናት ስልጣን ከተቆጣጠሩት አንዱ በሆኑት ዩዌሪ ሙሴቪኒና በታዋቂው ሙዚቀኛ ቦቢ ዋይን መካከል ከፍተኛ ፉክክር ይጠበቃል።

ሙዚቀኛው እና ለእጬ ፕሬዚዳንትነት የሚወዳደረው ቦቢ ዋይን፥ የኢንተርኔት መቋረጥ ምርጫውን የማጭበርበር አካል እንደሆነ ገልጿል።

"የኡጋንዳ ህዝብ በከፍተኛ ፅናትና ውሳኔ ላይ ነው። ይህንን ጨቋኝ መንግሥት ከስልጣን ለማውረድ የሚያግደው ኃይል አይኖርም።" ብሏል። ~ BBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia