TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#USA

የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን #በአየር_ንብረትና #በጤና ዙርያ የቀረቡ ረቂቅ ሕጎች ላይ ፊርማቸውን እንዳኖሩ ቢቢሲ ዘግቧል።

ባይደን በፊርማቸው ያጸኑት ሕግ በሃብታሞች ላይ ጠንከር ያለ ግብር የሚጥል ነው።

ይህ ረቂቅ ሕግ ከፍተኛ ገቢ ባላቸው ኩባንያዎች ላይ ግብር በመጣል በአየር ንብረት ለውጥና በጤና ዙርያ ለሚሠሩ ሥራዎች የሚውል ገንዘብ የሚያስገኝ እንዲሆን የተዘጋጀ ነው ተብሏል።

ጆ ባይደን ትናንት በረቂቅ ሕጉ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ሕግ እንዲሆን አጽንተውታል።

ይህ ሕግ ከዚህ ወዲያ በጤና ዙርያ በሐኪም የሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ እንዲስተካከል የሚያደርግ ነው።

የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ለዓመታት በሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ ላይ #ቅናሽ እንዲደረግ ሲወተውቱ የቆዩትን ጥያቄ ይመልሳል ተብሏል።

ተጨማሪ : https://telegra.ph/BBC-08-17

@tikvahethiopia
👍26613🙏7👎6🥰4