TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AviationAcademy

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን አካዳሚ በኮቪድ - 19 ወረርሽኝ ምክንያት አቋርጦት የነበረውን የገፅ ለገፅ ትምህርት መስጠት ጀምሯል።

በክፍል ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች ቁጥር በግማሽ እንዲቀንስ ተደርጓል፤ የተግባር ስልጠናውም አካላዊ ርቀት ተጠብቆ እየተሰጠ ነው ብሏል።

አካዳሚው የገፅ ለገፅ ትምህርቱን በሚሰጥበት ወቅት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከል የሚያግዙ መንገዶችን የማይተገብሩ ሰልጣኞችን #እንከማባረር የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ አሳስቧል።

አካዳሚው በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት የባከነውን የስልጠና ጊዜ ለማካካስ በሚል ተማሪዎቹን ጫና ውስጥ እንደማይከት ገልጾ ፤ በስልጠናው ተማሪዎች ማወቅ ያለባቸውን እውቀት ሁሉ እንዲያገኙ የስልጠና ጊዜው ወደፊት እንደሚገፋ አሳውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን አካዳሚ ፦
- በአውሮፕላን አካልና ሞተር ጥገና
- በአብራሪነት
- በበረራ አስተናጋጅነት
- በማርኬቲንግ እና ሊደርሺፕ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ታሳቢ በማድረግ ለ1 ሺህ 500 ሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ~(ኢቢኤስ፣የኢትዮጵያ አየር መንገድ)

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia