TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የእርቀ_ሰላም_ኮንፈረንስ

የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳደር እንዲሁም ኧሌ ልዩ ወረዳ አስተዳደር በአንድ ላይ ተባብረው የተፈጠረውን ግጭት በእርቅ ለመፍታት የእርቀ ሰላም ኮንፈረንስ አዘጋጅተዋል።

ይኸው ኮንፈረንስ ዛሬ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

ትላንት ለዚሁ የእርቀ ሰላም ኮንፈረንስ ዝግጅት የክልሉ ማርሽ ባንድ በካራት ከተማ ትዕይንት አቅርቧል።

በእርቀ ሰላም ኮንፈረንሱ ላይ ከሁለቱም መዋቅሮች ከሁሉም ቀበሌዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ፣ ከአጎራባች ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች የተጋበዙ እንግዶች፣ የክልል እና የፌዴራል ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ይሳተፉበታል ተብሏል።

መረጃው የኮንሶ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia