TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" የተሰረቀ ስልካችሁን ማስረጃ በማቅረብ መውሰድ ትችላላችሁ " - ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ የተሰረቁ ሞባይል ስልኮችን ከሌቦች የሚረከብ ግለሰብን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው ማሞ ድልድይ አካባቢ ግንቦት 4/2016 ዓ/ም ከማለዳ 12 ሰዓት ከ20 ላይ አንድ ግለሰብ ሞባይል ስልክ መቀማታቸውን ገንደ ቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡

ፖሊስ ጣቢያው ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ ባደረገው ክትትል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ከሌቦቹ ላይ የሚረከብ " ታምራት ፍቅረማርያም " የተባለን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡

በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ባደረገው ብርበራ በእለቱ የተሰረቀውን የሞባይል ስልክና በልዩ ልዩ ጊዚያት ከሌቦች የተረከባቸውን ፦
➡️ 61  ስማርት ሞባይል ስልኮችን ፣
➡️ 251 የታብሌት ስልክ ሽፋኖችን ፣
➡️ 2 ላፕቶፖችን እና በጥሬ 60 ሺ አንድ መቶ ብር ከሌባ ተቀባዩ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ መያዙን አስታውቋል፡፡

ግለሰቡ የተሰረቁ ሞባይል ስልኮችን እና ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ከሌቦች ተቀብሎ የሚያስቀምጠው በተከራየው ቤት ውስጥ ነው ተብሏል።

ቤት የሚያከራዩ ግለሰቦች የተከራይን ማንነነት እና በምን ስራ ላይ እንደተሰማራ የማረጋገጥ ግዴታ እንደለባቸው ፖሊስ አሳስቧል።

" የሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል / ተሰርቂያለሁ " የሚል ማንኛውም ግለሰብ ገንደ ቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ስልኩን በመለየትና አስፈላጊውን ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መረከብ እንደሚችል ተገልጿል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
👏1.75K290🙏110🤔83😢46😱38😡34🕊32🥰28😭25
#AddisAbaba

ጓደኛቸውን #በመግደል ሲያሽከረክረው የነበረውን መኪና ወስደው ተሰውረዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች ተያዙ።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ግንቦት 8 ቀን 2016 ዓ/ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሰሜን ማዘጋጃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡

ገ/ሚካኤል ሰይፉ የተባለው ሟች የወንጀል ፈፃሚዎቹ የቅርብ ጓደኛ ነው።

ጓደኛማቻቾቹ በየዕለቱ እየተገናኙ አብረው የሚውሉ፣ የሚዝናኑ እና በእጅጉ የጠነከረ የጓደኝነት ግንኙነት ያላቸው የሱሉልታ ከተማ ነዋሪዎች እንደሆኑ  ተጠርጣሪዎቹ ለፖሊስ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል።

በዕለቱ ሟች በወንጀሉ ከተጠረጠሩት ከሁለቱ ጓደኞቹ ጋር አብሮ ሲዝናና እንዳመሸ ታውቋል።

ተጠርጣሪዎቹ  ቴዎድሮስ ታከለ እና  ሲሳይ ጥላሁን ከምሽቱ 5 ስዓት ገደማ የጓደኛቸውን  አንገት በማነቅ ህይወቱ እንዲያልፍ ካደረጉ በኋላ አስክሬኑን መንገድ ላይ በመጣል  ሞባይል ስልኩንና መታወቂያውን ጨምሮ በወቅቱ ሲያሽከረክረው የነበረውን የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 4-15624 ኢት መኪና ወስደው ተሰውረዋል።

ፖሊስ የወንጀሉ ሪፖርት ከደረሰው በኋላ ባደረገው ያልተቋረጠ ክትትል ወንጀሉን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩትን ግለሰቦች ለይቶ በማወቅ በ24 ሰዓታት ውስጥ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል፡፡

አንደኛው ተጠርጣሪ ከአየር ጤና አካባቢ የተያዘ ሲሆን ሁለተኛው ተጠርጣሪ ደግሞ ሱሉልታ ከተማ ውስጥ ሊገኝ ችሏል፡፡

ፖሊስ ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ ካበናወነው ምርመራ የማስፋት ስራ የሰረቁትን ተሽከርካሪ በሸገር ከተማ " ወለቴ " ተብሎ ወደሚጠራው አካባቢ በመውሰድ እንዲሸጥላቸው ለአንድ ግለሰብ እንደሰጡት አረጋግጧል።

መኪናውም ከቆመበት በምሪት እንዲመለስ ተደርጓል፡፡

ተሽከርካሪውን ለመሸጥ ተስማምቶ ከተጠርጣሪዎቹ የተቀበለውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ለማወል ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
😭1.91K206👏125😡112😱102🙏60😢58🕊51🤔33🥰20
#እንድታውቁት #AddisAbaba

በመንገድ ኮሪደር ልማትና በአስፓልት የማንጠፍ ስራ ምክንያት ከመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ የሚወስደው ዋናው መንገድ በከፊል ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

መዚህ መሰረት ፡-

- ከለገሐር በመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ

- ከእስጢፋኖስ በቀጥታ ወደ ቦሌ አየር መንገድ

- ከኡራኤል በመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ

እንዲሁም #በውስጥ_ለውስጥ ወደ ዋናው ቦሌ አየር መንገድ የሚወስዱ መንገዶች ከዛሬ ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ #በየዕለቱ ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ከቀኑ 8:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:30 ሰዓት ለተሽከርካሪ በከፊል ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥማቸው ሌሎች አማራጭ መንገዶችን መጠቀም እንዳለባቸው አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
😡601216👏76🙏61😢31😭29🤔23🕊18🥰13😱1
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ነገ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።

የ1445ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ነገ ይከበራል።

የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅም ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

የሶላት ስነስርዓቱ የሚካሄደው በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ላይ ነው።

ይህ ተከትሎ ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የሶላት ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

በዚህም መሰረት ፦

- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ

- ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው አጎና ሲኒማ ላይ

- ከሜክሲኮ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ

- ከብሔራዊ ቤተመንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት ላይ

- ከኦሎሚፒያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

- ከመገናኛ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ 22 መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ

- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ለገሀር የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል አጠገብ

- ከሲግናል እና ከአቧሬ ወደ ካዛንቺስ የሚመጣው መንገድ አቧሬ ሴቶች አደባባይ ላይ

- ከመስቀል ፍላወር ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጣው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

- ከቄራ በአዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን መገንጠያ ላይ

- ከጌጃ ሰፈር በሰንጋተራ ወደ ለገሐር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ

- ከአብነት በጌጃ ሰፈር ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ አጠገብ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ሜትሮሎጂ መ/ቤት ላይ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚሄዱ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ አካባቢ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ወደ ለገሐር ለሚሄዱ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛው ላይ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ቀርቧል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
1.02K😡163🕊69🙏60👏56😭33🥰29😢29😱28🤔21
" የሞባይል ስልክ እና ላፕቶፕ ጠፍቶብኛል የሚል ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መረከብ ይችላል " - ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ በቴክኖሎጂ በመደገፍ ባደረገው ክትትል ግምቱ 150 ሺህ ብር የሚያወጣን ሞባይል ስልክን ከሌባ ላይ የገዛችን ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውሎ ንብረቱን ማስመለሱን አስታወቀ፡፡

ግለሰቧ ከወንጀለኞች በተለያየ ጊዜ የገዛቻቸው ልዩ ልዩ ሞባይል ስልኮችን ፣ ላፕቶፖችንና ታብሌት ይዞ ምርመራው መቀጠሉን አዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆል፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው ...
    
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው " አለምነሽ ፕላዛ " አካባቢ አንድ ግለሰብ  ግምቱ 150 ሺህ ብር የሚያወጣ አይነቱ አይፎን ፕሮ ማክስ ሞባይል ስልክ ይቀማሉ።

ይህን ተከትሎ አደይ አበባ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታሉ።

የግለሰቡን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ፖሊስ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሌሎች መንግስታዊ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በቴክኖሎጂ በመደገፍ ባደረገው ክትትል የተሰረቀው ስልክ አራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ከሚገኝ አንድ የሞባይል መሸጫ ሱቅ መኖሩ ይረጋገጣል፡፡

ፖሊስ የህግ አግባብን በመከተል ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትእዛዝ በማውጣት ባደረገው ብርበራ ከግለሰቡ ላይ የተቀማውን ስልክ ጨምሮ በልዩ ልዩ ጊዜያት ከተለያዩ ቦታዎች የተሰረቁ ፦

➡️ 85 ስማርት ሞባይል ስልኮችን  ፣

➡️ 4 ለፕቶፖችን ፣

➡️ 1 ታብሌትና የላፕቶፕ ቦርሳዎችን በኤግዚቢትነት ይዟል።

የቅሚያ ወንጀል የፈፀመውን ተጠርጣሪ ለመያዝ ክትትሉ መቀጠሉን ፖሊስ አመልክቷል።

የሞባይል ስልክ እና ላፕቶፕ ጠፍቶብኛል የሚል ማንኛውም ግለሰብ አደይ አበባ ስቴዲዮም አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ሞባይል ስልኩን በመለየትና  ትክክለኛ ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መረከብ  እንደሚችል አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

#AddisAbabapolice

@tikvahethiopia
601👏366🙏63🤔33😢27🕊16😭14😡14😱11🥰7
" ' ሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል ' የሚል ግለሰብ ማስረጃ በማቅረብ ስልኩን መውሰድ ይችላል " - ፖሊስ

በአዲስ አበባ በሞተር ሳይክል እየተንቀሳቀሱ ከግለሰቦች ሞባይል በመንጠቅ ሱቅ ውስጥ ሲያከመቹ የነበሩ 4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

አቶ ሱራፌል ቢያብል የተባሉ የግል ተበዳይ በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14  ዋና ስራ አስፈፀሚ ሲሆኑ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም  በክፍለ ከተማው ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ እየተሰራ ያለውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ እያደረጉ ነበር።

በወቅት 2 ተጠርጣሪዎች በጥቁር ሞተር ሳይክል ኮድ 2 A19216 ደ.ሕ (ደቡብ ህዝብ) በሆነ 1ኛ ተጠርጣሪ እያሽከረከረ ፣ 2ኛ ተጠርጣሪ ሞተር ሳይክል ላይ ከኋላ በመሆን ከግለሰቡ  ሞባይል ስልክ ነጥቀው በፍጥነት እያሽከረከሩ ከአካባቢው ይሰወራሉ።

የግል ተበዳይ ወንጀሉ እንደተፈፀመባቸው በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለገርጂ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ያመለክታሉ።

ፖሊስም የግል ተበዳዩን አቤቱታ በመቀበል  ባደረገው ክትትል ከሁለቱ ተጠርጣሪዎች በተጨማሪ ከሌቦቹ የሚረከቡ 2 ተጠርጣሪዎች  በድምሩ  4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል።

ህግን ተከትሎ ባደረገው ብርበራ ተጠርጣሪዎቹ ተከራይተው የሞባይል ጥገና የሚሰሩበት ሱቅ ውስጥ በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ ግለሰቦች ተቀምተው የተከማቹ 32 ስማርት ሞባይል ስልኮችን በኤግዚቢት ተይዘዋል።

" ሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል " የሚል ማንኛውም ግለሰብ በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያያ በአካል  በመቅረብና ትክክለኛ ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መውሰድ እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
👏890164🙏51😡40😱31🕊26😭17😢15🤔13🥰6
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰኔ 17/2016 ዓ/ም አንዲት መና ከበደ የተባለች የ26 ዓመት ወጣት ሴትን በመኪና ስርቆት ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ስር አውሏል።

ፖሊስ፥ ግለሰቧ ጥዋት 12:30 ገደማ ' ቤተል ቢጫ ፎቅ ' አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-B32912 አ.አ የሆነች ተሽከርካሪን የግል ተበዳይ መኖሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ሞተር ሳያጠፋ አቁሞት ጃኬት ለመደረብ በገባበት ይዛ መሰወሯንና ከግማሽ ቀን ፍለጋ በኋላ ሰሚት አካባቢ መያዟን አስረድቷል።

ፖሊስ ግለሰቧንም ከነተሽከርካሪው ፎቶ በማንሳት አሰራጭቷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ግለሰቧን እናውቃታለን ያሉ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ፤ መኪናውን መውሰድ አለመውሰዷን በግልጽ ባያሰፍሩም የሃብታም ልጅ እንደሆነች ፣ ስህተት እንደተፈጠረና ከወንጀሉ ነጻ ተብላ ወደ ቤት መግባቷን ጽፈዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ በተሽከርካሪ ስርቆት የተጠረጠረችው ግለሰብ መና ከበደ ክስ እንደተመሰረተባት አሳውቋል።

በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት መቅረቧንም አመልክቷል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ግለሰቧ ተሽከርካሪውን በመስረቋ ፓሊስ ምርመራ አጣርቶ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ልኮ ክስ እንዲመሰረትባት ማድረጉን አስረድቷል።

" በአንዳንድ  ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ' ግለሰቧ ተለቃለች ' እና ' ወንጀሉን ሳታውቅ ነው የፈፀመችው ' የሚሉ መረጃዎች እየተሰራጩ  ይገኛል " ያለው ፖሊስ የግል ተበዳይ መኪናቸው መሰረቁን ለፖሊስ እንዳመለከቱ ግለሰቧም ተሽከርካሪውን ለረጅም ሰዓት ይዛ መሰወሯ  ታሳቢ በማድረግና ድርጊቷም በማስረጃ በመረጋገጡ ዓቃቤ ህግ በተሽከርካሪ ስርቆት ክስ መመስረቱን አሳውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
👏550122😡60🤔47🙏26😭25😱24😢18🥰15🕊14
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ነገ ለስራ ይሁን ዘመድ ጥየቃ ወይም ደግሞ ለተለያየ ፕሮግራም ከቤት የምትወጡ ካላችሁ የሚዘጉ መንገዶች ይኖራሉ።

መንገዶች የሚዘጉት  80ኛውን የመቻል ስፖርት ቡድን ምስረታን ምክንያት በማድረግ በሚካሄድ የጎዳና ላይ ሩጫ ነው።

ሩጫው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።

በዚህም ፦

- ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ

- ከካዛንቺስ ወደ ባምቢስ

- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ

- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት

- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ

- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ አንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
😡759158🙏156😭37👏34😢19🕊18🤔17😱17🥰13
#AddisAbaba

አዲስ አበባ ፖሊስ ከሰኔ 5 እስከ ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ/ም ለ15 ቀናት በሁሉም ክ/ከተሞች ኦፕሬሽን ማካሄዱን አሳውቋል።

በርካታ የወንጀል ተጠርጣሪዎችንና ኤግዚቢቶችን በቁጥጥር ስር እንዳዋለም ገልጿል።

በተደረገው ኦፕሬሽን ፦
➡️ ከዚህ ቀደም የተሰረቁ 8 የተለያዩ ተሽከርካሪዎች ማስመለሱን ፤
➡️ ለወንጀል ፈፃሚዎቹ ሀሰተኛ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በተለጣፊ እስቲከር ሲያዘጋጁ የነበሩ ግለሰቦች ሀሰተኛ ሰሌዳ ለማዘጋጀት ከሚጠቀሙበት ኮምፒውተር ፣ ላፕቶፕ ፣ ፍላሽ እና ካሜራ ጋር በቁጥጥር ስር እንዳዋለ፤
➡️ የመኪና መያቸውን
➡️ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም የቅሚያ ወንጀል የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን ይዞ ከ700 በላይ ሞባይል ስልኮች ማስመለሱን፤
➡️ የተሰረቀ እቃ ከሚገዙ ህገወጦች ላይ 108 ላፕቶፕ ߹6 ኮምፒዩተር ߹11 ካሜራዎች ߹ 2 ቴሌቪዥንና የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ከሸሸጉበት ቦታ መያዙን
➡️ 2 ክላሽ ከመሰል 120 ጥይቶች ጋር፣ 67 ልዩ ልዩ ሽጉጦች ከ568 መሰል ጥይት ጋር እንዲሁም 2 ኋላ ቀር መሳሪያ ከእነ ተጠርጣሪዎቹ በኦፕሬሽኑ መያዙን አመልክቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ኮንትሮባንድ ፣ ሀሰተኛና ሰነዶችን እና መድኃኒቶች በኦፕሬሽኑ መገኘታቸውን ገልጿል።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንደሚኒዬም ውስጥ መድሃኒት የማከፋፈልም ሆነ የመሸጥ ፍቃድ የሌላቸውና በህገ-ወጥ መንገድ መድሃኒት እያዘጋጁ ሲያከፋፍሉ የተገኙ ግለሰቦች ተዘዋል፡፡

ግለሰቦቹ ያዘጋጇቸውና ለገበያ ሊያቀርቧቸው የነበሩ ፦
° 169 ብልቃጥ መድሃኒቶች ፣
° 40 ግሉኮስ ፣
° በርካታ የመድሃኒት ብልቃጦች እና ህገ-ወጥ ስራቸውን ለመስራት የሚገለገሉበት አንድ ማሽንን ጨምሮ ፕሪንተር እና ላፕቶፕ በኤግዚቢትነት መያዙን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
🙏37798👏80😢14🕊13😡13😱11😭10🥰5🤔5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ህፃን ሶሊያን ዳንኤል ተገኝታለች። • " 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ ልትሰወር መቻሏል ተጠርጣሪዋ ገልጻለች " - የአዲስ አበባ ፖሊስ ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ባደረገው ጠንካራ ክትትል ሱሉልታ ከተማ ላይ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።…
#AddisAbaba

የሁለት ዓመቷን ሶሊያና ዳንኤል የተባለችውን ህፃን በመጥለፍና በከባድ ስርቆት ወንጀል የተከሰሰችው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥታለች።

የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባት ቤዛዊት በቀለ የተባለችው ግለሰብ በሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራበት ከነበረበት ቤት (ሳሪስ አዲስ ሰፈር) መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ/ም ህጻን ሶሊያናን ይዛ በመሰወር ሱሉልታ ከተማ " ኖኖ መና አቢቹ " ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህፃኗን ሸሽጋ በተቀመጠችበት በአዲስ አበባ ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሏን ይታወሳል።

ግለሰቧ በቁጥጥር ስር ከዋለች በኃላ የአ/አ ፖሊስ ምርመራ የማስፋት ስራ በመስራት ከዚህ ቀደም በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረችባቸው አምስት የተለያዩ ቤቶች ልዩ ልዩ ንብረቶችን መስረቋን አረጋግጧል።

ከሰረቀቻቸው ንብረቶች መካከልም 2 ላፕቶፕ ፣ 1 ሞባይል ስልክ እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎች ፖሊስ ባደረገው ጥረት ከሸጠችበት በምሪት እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡

በግለሰቧ ላይ ምርመራ ተጣርቶ በከባድ ስርቆት እና ህፃን ልጅ መጥለፍ በሚል ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ቤዛዊት በቀለ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
👏714123🙏46😢37😭26🕊14😱12🤔9😡7🥰4