#ታሽገዋል
ዋልያ ቆዳ ፋብሪካ እንዲሁም አዲስ አበባ ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር የአካባቢ እና የህብረተሰቡን ጤና የሚጎዳ ብክለት በማድረሳቸዉ ምክንያት ታሸጉ።
በአቃቂ ቃሊቲ እና በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ የሚገኙት ሁለቱ ፋብሪካዎች የሚለቁት ከፍተኛ የሆነ ያልታከመ አደገኛ ፈሳሽ ቆሻሻ በአካባቢዉ ላይ ብክለት እያደረሰ እንደሚገኝ ህብረተሰቡ አቤቱታዎችን ሲያቀርብ ነበር።
የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የአካባቢ ብክለት ኢንስፔክሽን ባለሙያዎችም በመስክ ባደረጉት ምልከታ ይህንን ማረጋገጥ ችለዋል።
ይህ መረጃ ከአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የተገኘ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዋልያ ቆዳ ፋብሪካ እንዲሁም አዲስ አበባ ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር የአካባቢ እና የህብረተሰቡን ጤና የሚጎዳ ብክለት በማድረሳቸዉ ምክንያት ታሸጉ።
በአቃቂ ቃሊቲ እና በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ የሚገኙት ሁለቱ ፋብሪካዎች የሚለቁት ከፍተኛ የሆነ ያልታከመ አደገኛ ፈሳሽ ቆሻሻ በአካባቢዉ ላይ ብክለት እያደረሰ እንደሚገኝ ህብረተሰቡ አቤቱታዎችን ሲያቀርብ ነበር።
የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የአካባቢ ብክለት ኢንስፔክሽን ባለሙያዎችም በመስክ ባደረጉት ምልከታ ይህንን ማረጋገጥ ችለዋል።
ይህ መረጃ ከአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የተገኘ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ በከተማው ውስጥ በአዋኪ ድርጊቶች ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን ሆቴሎች እና ላውንጆች እንዲታሸጉ ማድረጉን አስታወቀ።
አስተዳደሩ ፤ በትናንትናው እለት ከምሽቱ 4፡00 እስከ ለሊቱ 8.30 በፀጥታ ግብረ ሀይል (ኦፕሬሽኑ ላይ የተሳተፉየአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ የሠላምና ፀጥታ ፣የደንብ ማስከበር) ተወስዷል ባለው እርምጃ ፦
በቂርቆስ ክ/ከተማ ፦
1. ሪቮ አዲስ ላወንጅ :- 87 የሺሻ ዕቃና በድርጊቱ ተሳታፊ 200 ወጣቶች
2. አቤም ሆቴል 22 የሺሻ ዕቃና 8 ወጣቶች
3. ናሽናል ሆቴል 16 የሺሻ ዕቃና 67 ወጣቶች
4. ሞሲሳ ሆቴል 7 የሺሻ እቃ
በቦሌ ክ/ከተማ ፦
5. ቀነንሳ ሆቴል 35 የሺሻ እቃ
6. ዘባንክ ላውንች 28 የሺሻ እቃ
የካ ክ/ከተማ ፦
7. ቤልቪው ሆቴል 86 የሺሻ ዕቃ እና 54 ሠው የተያዘ በሶስቱ ክ/ከተሞች በጥቅሉ 7ቱ ቤቶች #ታሽገዋል።
በተጨማሪ ፤ 281 የሺሻ እቃ እና 330 ሰው በቁጥጥር ስር ከተደረጉ በኋላ 200 ወጣቶች በምክር እንዲለቀቁ መደረጉን 130 ሰዎች ግን በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑን አመልክቷል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ በከተማው ውስጥ በአዋኪ ድርጊቶች ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን ሆቴሎች እና ላውንጆች እንዲታሸጉ ማድረጉን አስታወቀ።
አስተዳደሩ ፤ በትናንትናው እለት ከምሽቱ 4፡00 እስከ ለሊቱ 8.30 በፀጥታ ግብረ ሀይል (ኦፕሬሽኑ ላይ የተሳተፉየአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ የሠላምና ፀጥታ ፣የደንብ ማስከበር) ተወስዷል ባለው እርምጃ ፦
በቂርቆስ ክ/ከተማ ፦
1. ሪቮ አዲስ ላወንጅ :- 87 የሺሻ ዕቃና በድርጊቱ ተሳታፊ 200 ወጣቶች
2. አቤም ሆቴል 22 የሺሻ ዕቃና 8 ወጣቶች
3. ናሽናል ሆቴል 16 የሺሻ ዕቃና 67 ወጣቶች
4. ሞሲሳ ሆቴል 7 የሺሻ እቃ
በቦሌ ክ/ከተማ ፦
5. ቀነንሳ ሆቴል 35 የሺሻ እቃ
6. ዘባንክ ላውንች 28 የሺሻ እቃ
የካ ክ/ከተማ ፦
7. ቤልቪው ሆቴል 86 የሺሻ ዕቃ እና 54 ሠው የተያዘ በሶስቱ ክ/ከተሞች በጥቅሉ 7ቱ ቤቶች #ታሽገዋል።
በተጨማሪ ፤ 281 የሺሻ እቃ እና 330 ሰው በቁጥጥር ስር ከተደረጉ በኋላ 200 ወጣቶች በምክር እንዲለቀቁ መደረጉን 130 ሰዎች ግን በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑን አመልክቷል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
@tikvahethiopia