TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ታሽገዋል

ዋልያ ቆዳ ፋብሪካ እንዲሁም አዲስ አበባ ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር የአካባቢ እና የህብረተሰቡን ጤና የሚጎዳ ብክለት በማድረሳቸዉ ምክንያት ታሸጉ።

በአቃቂ ቃሊቲ እና በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ የሚገኙት ሁለቱ ፋብሪካዎች የሚለቁት ከፍተኛ የሆነ ያልታከመ አደገኛ ፈሳሽ ቆሻሻ በአካባቢዉ ላይ ብክለት እያደረሰ እንደሚገኝ ህብረተሰቡ አቤቱታዎችን ሲያቀርብ ነበር።

የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የአካባቢ ብክለት ኢንስፔክሽን ባለሙያዎችም በመስክ ባደረጉት ምልከታ ይህንን ማረጋገጥ ችለዋል።

ይህ መረጃ ከአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ በከተማው ውስጥ በአዋኪ ድርጊቶች ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን ሆቴሎች እና ላውንጆች እንዲታሸጉ ማድረጉን አስታወቀ።

አስተዳደሩ ፤ በትናንትናው እለት ከምሽቱ 4፡00 እስከ ለሊቱ 8.30 በፀጥታ ግብረ ሀይል (ኦፕሬሽኑ ላይ የተሳተፉየአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ የሠላምና ፀጥታ ፣የደንብ ማስከበር) ተወስዷል ባለው እርምጃ ፦

በቂርቆስ ክ/ከተማ ፦

1. ሪቮ አዲስ ላወንጅ :- 87 የሺሻ ዕቃና በድርጊቱ ተሳታፊ 200 ወጣቶች
2. አቤም ሆቴል 22 የሺሻ ዕቃና 8 ወጣቶች
3. ናሽናል ሆቴል 16 የሺሻ ዕቃና 67 ወጣቶች
4. ሞሲሳ ሆቴል 7 የሺሻ እቃ

በቦሌ ክ/ከተማ ፦

5. ቀነንሳ ሆቴል 35 የሺሻ እቃ
6. ዘባንክ ላውንች 28 የሺሻ እቃ

የካ ክ/ከተማ ፦

7. ቤልቪው ሆቴል 86 የሺሻ ዕቃ እና 54 ሠው የተያዘ በሶስቱ ክ/ከተሞች በጥቅሉ 7ቱ ቤቶች #ታሽገዋል

በተጨማሪ ፤ 281 የሺሻ እቃ እና 330 ሰው በቁጥጥር ስር ከተደረጉ በኋላ 200 ወጣቶች በምክር እንዲለቀቁ መደረጉን 130 ሰዎች ግን በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑን አመልክቷል።

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

@tikvahethiopia