TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኦነግ‼️

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በምርጫ ቦርድ እንዲመዘገብ የቀረበለትን ጥያቄ #አልቀበልም አለ መባሉን #አስተባበለ። ፓርቲው ለምርጫ ቦርድ የምዝገባ ጥያቄ አቅርቤያለሁ ብሏል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ #ቀጀላ_መርዳሳ በአርትስ ቴሌቪዠን ላይ ቀርበው እንደተናገሩት ኦነግ ምርጫ ቦርድ ቀርቤ አልመዘገብም አለ በሚል የሚናፈሱ መረጃዎች #ትክክል_አይደሉም ብለዋል። እንደአቶ ቀጀላ ገለጻ ኦነግ ምዝገባ ለማካሄድ ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቅርቧል። ነገር ግን የፓርቲዎች ምዝገባ መመሪያ ላይ የሰፈሩት ቅድመ ሁኔታዎች ድርጅቱ ለምርጫ ከሚያደርገው ዝግጅት ጊዜ መጣበብ እና ከድርጅቱ ታሪካዊ አመጣጥ ጋር ሊጣጣሙለት አልቻሉም።

የ45 ዓመታት የምስረታ ታሪክ ያለው ኦነግ በአዲስ ሁኔታ 1500 ሰዎችን አስፈርሞ ለምዝገባ እንዲቀርብ መጠየቁ ድርጅቱን እንደአዲስ የመቁጠር ያህል ነው ያሉት አቶ ቀጀላ ኦነግን በአዲስ አባላትና ደጋፊዎች ማዋቀርም የመስራች አባላቱን ታሪክ መፋቅ ነው ብለዋል።

ኦነግ በአሁኑ ወቅት ወደኢትዮጵያ የመጣው በፖለቲካ ውሳኔ መሆኑን የተናገሩት ከፍተኛ አመራሩ ይህም በይፋ እውቅና የተሰጠው ድርጅት መሆኑን ይመሰክራል ነው ያሉት።

ምንጭ፦ አርትስ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍2