#የፖሊስ_ማሳሰቢያ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ በትራፊክ መብራቶች እና በመስቀለኛ መንገዶች ላይ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ንግድ እና የልመና ተግባራት ላይ በተሰማሩ ግለሰቦችና #ገንዘብ_በሚሰጡና በሚገበያዩ አሽከርካሪዎች ላይ በህጉ መሰረት ጠንካራ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ።
በልመና ለተሰማሩ ሰዎች ገንዘብ የሚሰጡ እና ግብይት የሚፈፅሙ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።
በሚኒስትሮች ም/ቤት የወጣው የትራንስፖርት መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/2009 #በትራፊክ_መብራት ላይ ወይም #በመስቀለኛ_መንገድ ላይ በልመና ተግባር ለተሰማሩ ሰዎች ገንዘብ የሰጠ ወይም ግብይት የፈፀመ አሽከርካሪ ቅጣት እንደሚጣልበት ይደነግጋል፡፡
" ይሁን እንጂ #የአሽከርካሪዎች ደንብ አክባሪ አለመሆን በእነዚህ መንገዶች ላይ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ንግድና የልመና ተግባራት እንዲስፋፉ ምክንያት ሆኗል " ሲል ፖሊስ ገልጿል።
የትራፊክ ደንቡ አለመከበር #ለትራፊክ_አደጋ መጨመር እና ጤናማ የትራፊክ ፍሰት እንዳይኖር እንቅፋት ከመፍጠሩ ባሻገር በተለይ የትራፊክ መብራቶች ባሉባቸው ጎዳናዎች የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች የሚፈፀምባቸው ቦታዎች እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ አስረድቷል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/Addis-Ababa-Police-01-04
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ በትራፊክ መብራቶች እና በመስቀለኛ መንገዶች ላይ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ንግድ እና የልመና ተግባራት ላይ በተሰማሩ ግለሰቦችና #ገንዘብ_በሚሰጡና በሚገበያዩ አሽከርካሪዎች ላይ በህጉ መሰረት ጠንካራ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ።
በልመና ለተሰማሩ ሰዎች ገንዘብ የሚሰጡ እና ግብይት የሚፈፅሙ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።
በሚኒስትሮች ም/ቤት የወጣው የትራንስፖርት መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/2009 #በትራፊክ_መብራት ላይ ወይም #በመስቀለኛ_መንገድ ላይ በልመና ተግባር ለተሰማሩ ሰዎች ገንዘብ የሰጠ ወይም ግብይት የፈፀመ አሽከርካሪ ቅጣት እንደሚጣልበት ይደነግጋል፡፡
" ይሁን እንጂ #የአሽከርካሪዎች ደንብ አክባሪ አለመሆን በእነዚህ መንገዶች ላይ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ንግድና የልመና ተግባራት እንዲስፋፉ ምክንያት ሆኗል " ሲል ፖሊስ ገልጿል።
የትራፊክ ደንቡ አለመከበር #ለትራፊክ_አደጋ መጨመር እና ጤናማ የትራፊክ ፍሰት እንዳይኖር እንቅፋት ከመፍጠሩ ባሻገር በተለይ የትራፊክ መብራቶች ባሉባቸው ጎዳናዎች የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች የሚፈፀምባቸው ቦታዎች እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ አስረድቷል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/Addis-Ababa-Police-01-04
@tikvahethiopia
👍1.47K👎344❤51😢44🕊36🥰22🙏22😱21
“ አንድ ቀን አሽከርካሪዎች ችግር መንገድ ላይ ገጥሟቸው በሚቆሙበት ሰዓት ፤ የሆነ ነገር ብሷቸው ከሥራ ቢገለሉ የመጀመሪያው ተጎጂ ህብረተሰቡ ነው ” - የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር
➡️ “ አሽከርካሪዎችን ሁሉም ይንከባከብ !! ”
“ ሹፌሮች ብሷቸው ከስራ ቢገለሉ ” ተጎጂው ማህበረሰቡ በመሆኑ፣ ሁሉም አካል አሽከርካሪዎችን ሊንከባከብ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳሰበ።
“ አንድ ቀን አሽከርካሪዎች ችግር መንገድ ላይ ገጥሟቸው በሚቆሙበት ሰዓት የሆነ ነገር ብሷቸው ከሥራ ቢገለሉ የመጀመሪያው ተጎጂ ህብረተሰቡ ነው ” ሲል አስጠንቅቋል።
አሽከርካሪዎች ከሥራ ቢገለሉ የነዳጅ፣ መድኃኒት፣ ምግብ፣ ዘይት፣ ሸቀጣሸቀጥ ግብዓት ማግኘት እንደማይቻል፣ ግብይቱ እንደሚዛባ ገልጾ፣ ማህበረሰቡ ከአሽከርካሪዎች ጎን እንዲቆም አስገንዝቧል።
ማኀበሩ፣ “ይህንን ያልተረዱ የመንግስት አካላት ግንዛቤ ኖሯቸው ህግን ያስከብሩ፣ ህገ ወጥ አሽከርካሪዎች ካሉም በህግ ይጠየቁ። ከዚያ ውጭ ያሉ እንቅስቃሴን የሚገድቡ ነገሮችን ባያደርጉብን ” ሲልም አክሏል።
“ በተለይ የገቢ ወጭ ንግድን ማቋረጥ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቁ እንቅፋት ስለሚሆን ሎጂስቲኩንም ስለሚያናጋው አሽከርካሪዎችን ሁሉም አካል ይንከባከብ ” ነው ያለው።
“ አሽከርካሪዎች ለኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ እንቅስቃሴ ወሳኝ አምድ ናቸው። እነሱ ከሌሉ ምንም ነገር ይቆማል ” ሲል አስጠንቅቋል።
ማኀበሩ፣ “ ስለዚህ ከህብረተሰቡ ጀምሮ እስከላይ ያለው አካል ጥቅማቸውንና አገልግሎታቸውን ተረድቶ በሚሄዱበት ሁሉ ይጠብቃቸው የሚጓጉዙት የህብረተሰቡ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ነው ” ብሏል።
“ ሹፌር ተገደለ፣ መኪና ተቃጠለ ብቻ ሳይሆን ሁልጊዜ በየቀኑ እንደዜና ሁሉም ሚዲያዎች ” ፕሮግራም ይዘው የሹፌሮደችን ጉዳይ እንዲዘግቡ ተጠይቋል።
“ ለምሳሌ ግንቦት 9/2017 ዓ/ም የሹፌሮችን ቀን አክብረን ውለናል” ያለው ማኀበሩ፣ “ አንድም ሚዲያ አልመጣልንም። አንድ አርቲስት አልበም ሲያስመርቅ ማይክራፎኑ ይበዛል። ማይክሮፎን አርቲስቶቹ የሚዘፍኑበትንም ሁሉ ያመጣው ግን አሽከርካሪ ነው ” ሲል ማኀበሩ ወቅሷል።
“ የኢትዮጵያ ከባድ መኪናዎች አሽከርካሪ በኢትዮጵያ ሚዲያዎች በጠቅላላ አዝኗል። አንድ ሚድያ መጥቶ አልዘገበልንም። ይሄን ሚዲያዎች ትኩረት እንዲሰጡ ይደረግ ” ሲልም በአጽንኦት ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.66K🙏159👏62😭57🕊46🤔25😢19🥰10😱7