TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#FaceBook

ፌስ ቡክ #ከጥላቻ_ንግግር ፖሊሲው ጋር የሚጣረሱ መልዕክቶችን በቀጥታ በሚያሠራጩ ተጠቃሚዎች ላይ አዲስ የቁጥጥር ህግ ሊያስተዋውቅ ነው። በኒውዚላንድ ክሪስት ቸርች መስጊዶች ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ለተወሰነ ጊዜ ተጠቃሚዎችን ከፌስቡክ ማገድ እንደ አንድ የመፍትሔ ሃሳብ ቀርቧል። በፓሪስ በሚካሄደውና በፈረንሳዩ ፕሬዚደንት ኢማኑኤል ማክሮንና በኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን በሚመራው ጉባዔ ላይም ፅንፈኛና ተንኳሽ የሆኑ ንግግሮችን ለመቀነስ የሚረዱ ሃሳቦች ይቀርቡበታል ተብሏል። በመስጊዶቹ ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ በስፋት ከተሠራጨው ተንቀሳቃሽ ምስል በኋለ ፌስቡክ ትችት አጋጥሞታል። በኒውዚላንድ ክሪስትቸርች ከተማ ሁለት መስኪዶች ላይ በተከፈተ ተኩስ 49 ሰዎች ሲገደሉ ብዙዎች መጎዳታቸው ይታወሳል።

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#StopHateSpeech
#ከጥላቻ_ንግግር_እንቆጠብ!!
የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የውይይት መድረክ ከልዩ ልዩ ጥበባዊ ዝግጅቶች ጋር በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ነገ #ቅዳሜ እና #እሁድ በቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት አማካኝነት በግቢያችን ይካሄዳል።

#ፕሮግራሞች

#ቅዳሜ

☞ ብዙ ኪ.ሜ አቆራርጠው ለፍቅር እና ለሰላም ለሚመጡት የTIKVAH-ETH
ቤተሰብ አባላት ደማቅ አቀባበል ይደረጋል፣ ጥበባዊ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ።

#እሁድ

√የደም ልገሳ ፕሮግራም
√በርካታ ታዳሚዎች በተገኙበት ስለጥላቻ ንግግር ፅሁፎችን ይቀርባሉ ፤ ልዩ ልዩ
ኪነ ጥበባዊ ስራዎች ይቀርባሉ፡፡
√በግቢያችን የፅዳት ዘመቻ ይካሄዳል

#ዋቸሞ_ዩኒቨርሲቲ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
🥰1