TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Dexamethasone

'ዴክሳሜታሰን' የተባለው መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በሽታ በፅኑ የታመሙትን ሰዎች ህይወት ለመታገድ እንደሚረዳ የብሪታንያ ተመራማሪዎች ገለፁ።

ሳይንቲስቶቹ በህክምና ላይ ያሉና በቬንትሌተር የሚተነፍሱት ታማሚዎችን የመሞት እድል በአንድ ሶስተኛ እንደሚቀንስ የገለጹ ሲሆን በኦክስጅን ውስጥ ያሉትን የመሞት ዕድላቸውን በአንድ አምስተኛ እንደሚቀንስ ተናግረዋል፡፡

ይህ መድሃኒት የኮቪድ-19 ለማከም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተደረጉ ትልልቅ ሙከራዎች አንዱ መሆኑንም ነው የቢቢሲ ዘገባ የሚያመለክተው፡፡

ተመራማሪዎቹ የኮሮና ቫይረስ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ይህ መድሃኒት ጥቅም ላይ ውሎ ቢሆን ኖሮ የአምስት ሺ ሰዎችን ሕይወት ማትረፍ ይቻል እንደነበርም አስታውቀዋል፡፡

ይህ መድሃኒት (ዴክሳሜታሶን) ዋጋው በጣም አነስተኛ እና ለድሃ ሀገራትም ጭምር በቀላሉ ሊገዙት የሚችሉት መሆኑ ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ ቢቢሲ ፣ አል ዓይን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Dexamethasone

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በዴክሳሜታሶን መድሃኒት ዙሪያ የወጣውን ጆርናል የክሊኒካል አማካሪ ቡድናቸው እየገመገመው እንደሆነ ዛሬ ምሽት አሳውቀዋል።

የጤና ሚኒስትሯ በነገው ዕለት አንድ ድምዳሜ ላይ ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።

በመድሀኒቱ ዙርያ የቀረበው ማስረጃ ላይ ከስምምነት ላይ ከተደረሰ 'ዴክሳሜታሶን' በኢትዮጵያ በስፋት ስለሚገኝ ችግር አይሆንም ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia