TIKVAH-ETHIOPIA
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 169 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 5,798 የላብራቶሪ ምርመራ 169 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 1,805 ደርሷል፡፡ ቫይረሱ የተገኘባቸው 111 ወንድ እና 58 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ1 እስከ 78 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 168 ኢትዮጵያውያን እና…
ዓዲ ሓሩሽ የስደተኞች ካምፕ!
በትግራይ ክልል በሚገኘው 'የኤርትራ ስደተኞች ካምፕ' አንዲት ስደተኛ በኮሮና ቫይረስ መያዟ መረጋገጡን የክልሉ ጤና ቢሮ አሳውቋል።
ትላንት በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጠ 4 ሰዎች መካከል አንዷ ኤርትራዊት ስደተኛ መሆኗን የክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መቆጣጠር አስተባባሪ አቶ ሳሙኤል አረጋይ ለVOA ተናግረዋል።
አቶ ሳሙኤል እንደተናገሩት ቫይረሱ የተገኘባት በዓዲ ሓሩሽ የስደተኞች ካምፕ ነዋሪ የሆነችው የ16 ዓመት ሴት መሆኗን ነው የገለፁት።
ባለፈው ሳምንት ከሌሎች 26 የሚሆኑ ሰዎች ጋር በመሆን ወደ ፀበል ቦታ ተጉዛ እንደነበረም ለሬድዮ ጣቢያው ገልፀዋል።
ቫይረሱ የተገኘባት ወደ አክሱም የኮሮና ማዕከል ለመውሰድ እየተሰራ መሆኑና ከእሷ ጋር ግንኙነት የነበራቸውን ሰዎች በመለየት ወደ ማቆያ ማዕከል እየገቡ እንደሆነ ተናግረዋል።
ስደተኞች ካምፕ ለኮሮና መስፋፋት ተጋላጭ ከሆኑ ቦታዎች አንዱ በመሆኑ ይህንን መሰረት በማድረግ በዓዲ ሓሩሽ የስደተኞች መጠለያ በብዛት ሰዎች የመመርመር ስራ ይከናወናል ብለዋል።
ውጤቱንም በማየት አስፈላጊ ውስኔዎች ከሚመለከታቸው መንግስታዊ ተቋማት ጋር በመሆን ይሰራል ሲሉ #ለVOA ገልፀዋል።
የፌዴራል መንግሥት የስደተኞችና የስደት ተመላሾች ኤጄንሲ በበኩሉ በፌዴራሉ መንግሥት በሚመለከታቸው መሥሪያ ቤት በይፋ በስደተኞች ካምፕ ላይ በኮሮና የተያዘ ሰው እንዳለ የተገለፀ ነገር የለም ሆኖም ግን በስደተኞች መጠለያ ቫይረሱ ለመከላከል ከገባም ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው ብሏል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በትግራይ ክልል በሚገኘው 'የኤርትራ ስደተኞች ካምፕ' አንዲት ስደተኛ በኮሮና ቫይረስ መያዟ መረጋገጡን የክልሉ ጤና ቢሮ አሳውቋል።
ትላንት በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጠ 4 ሰዎች መካከል አንዷ ኤርትራዊት ስደተኛ መሆኗን የክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መቆጣጠር አስተባባሪ አቶ ሳሙኤል አረጋይ ለVOA ተናግረዋል።
አቶ ሳሙኤል እንደተናገሩት ቫይረሱ የተገኘባት በዓዲ ሓሩሽ የስደተኞች ካምፕ ነዋሪ የሆነችው የ16 ዓመት ሴት መሆኗን ነው የገለፁት።
ባለፈው ሳምንት ከሌሎች 26 የሚሆኑ ሰዎች ጋር በመሆን ወደ ፀበል ቦታ ተጉዛ እንደነበረም ለሬድዮ ጣቢያው ገልፀዋል።
ቫይረሱ የተገኘባት ወደ አክሱም የኮሮና ማዕከል ለመውሰድ እየተሰራ መሆኑና ከእሷ ጋር ግንኙነት የነበራቸውን ሰዎች በመለየት ወደ ማቆያ ማዕከል እየገቡ እንደሆነ ተናግረዋል።
ስደተኞች ካምፕ ለኮሮና መስፋፋት ተጋላጭ ከሆኑ ቦታዎች አንዱ በመሆኑ ይህንን መሰረት በማድረግ በዓዲ ሓሩሽ የስደተኞች መጠለያ በብዛት ሰዎች የመመርመር ስራ ይከናወናል ብለዋል።
ውጤቱንም በማየት አስፈላጊ ውስኔዎች ከሚመለከታቸው መንግስታዊ ተቋማት ጋር በመሆን ይሰራል ሲሉ #ለVOA ገልፀዋል።
የፌዴራል መንግሥት የስደተኞችና የስደት ተመላሾች ኤጄንሲ በበኩሉ በፌዴራሉ መንግሥት በሚመለከታቸው መሥሪያ ቤት በይፋ በስደተኞች ካምፕ ላይ በኮሮና የተያዘ ሰው እንዳለ የተገለፀ ነገር የለም ሆኖም ግን በስደተኞች መጠለያ ቫይረሱ ለመከላከል ከገባም ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው ብሏል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia