#update በባሕር ዳር ማረሚያ ቤት የሟቾች ቁጥር 5 ደረሰ፤ አንድ የፖሊስ አባልም የደረሰበት አልታወቀም፡፡ ትናንት በግምት ከቀኑ 7-8፡00 ባለው ጊዜ በባሕር ዳር ማረሚያ ቤት ግጭት መቀስቀሱና የ4 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ቀደም ብሎ ተዘግቦ ነበር፡፡ ዘግይቶ በወጣ መረጃ ደግሞ በግጭቱ የሟቾች ቁጥር 5 ደርሷል፤ የሟቾች አስከሬንም ለቤተሰቦቻቸው ተሰጥቷል፡፡ በሌላ በኩል አንድ የፖሊስ አባል እስካሁን #አልተገኘም፡፡ የተንቀሳቃሽ ስልኩ ማረሚያ ቤቱ ውስጥ መገኘቱንና የፖሊስ አባሉ ግን እስካሁን ያለበት ሁኔታና ቦታ አለመታወቁ በማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ኮማንደር #ውብሸት_መኮንን ተገልጿል።
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia