TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING በኢትዮጵያ ተጨማሪ 25 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 1,847 ላቦራቶሪ ምርመራ ሃያ አምስት (25) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር መቶ ሰማንያ ሰባት (187) ደርሷል። ዛሬ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ 24 ወንድ 1 ሴት እንዲሁም እድሜያቸው…
#AtoTemesgenHaile
በሀዲያ ዞን በኮሮና ቫይረስ መያዙ ስለተረጋገጠው አንድ (1) ሰው ዙሪያ ከሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተመስገን ኃይሌ የተገኘ አጭር መረጃ ፦
- በዞኑ ለኮሮና ቫይረስ ተጋላጭ ሆነዋል በሚል ተጠርጥረው በተዘጋጀው አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ከተደረጉት ውስጥ በ2ኛ ዙር ወደ ሀዋሳ የምርመራ ማዕከል ከተላከው የ10 ሰዎች ናሙና ውስጥ ነው አንድ ሰው በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠው።
- በኮቪድ-19 መያዙ የተረጋገጠው ግለሰብ በሀዲያ ዞን ሻሾጎ ወረዳ ሲሆን ወደ ደቡብ አፍሪካ ጉዞ ጀምረው ሞያሌ ቆይተው ወደ ዞኑ ከተመለሱና ከነርሱም መካከል በሀላባ ዞን በትራንስፖርት ሲጓዝ ተይዞ ለይቶ ማቆያ ውስጥ የሚገኘው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ከተረጋገጠው ግለሰብ ጋር የቀጥታ ግንኙነት የነበረው ነው።
- በዞኑ በኮሮና ቫይረስ መያዙ ከተረጋገጠው ግለሰብ ጋር በቀጥታም ሆነ በሌላ መንገድ ግንኙነት የነበራቸው 9/ዘጠኝ/ ሰዎች በመለየት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ወደተዘጋጀው ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ተደርገዋል።
- በአጠቃለይ በሀዲያ ዞን 51 ሰዎች በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሀዲያ ዞን በኮሮና ቫይረስ መያዙ ስለተረጋገጠው አንድ (1) ሰው ዙሪያ ከሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተመስገን ኃይሌ የተገኘ አጭር መረጃ ፦
- በዞኑ ለኮሮና ቫይረስ ተጋላጭ ሆነዋል በሚል ተጠርጥረው በተዘጋጀው አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ከተደረጉት ውስጥ በ2ኛ ዙር ወደ ሀዋሳ የምርመራ ማዕከል ከተላከው የ10 ሰዎች ናሙና ውስጥ ነው አንድ ሰው በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠው።
- በኮቪድ-19 መያዙ የተረጋገጠው ግለሰብ በሀዲያ ዞን ሻሾጎ ወረዳ ሲሆን ወደ ደቡብ አፍሪካ ጉዞ ጀምረው ሞያሌ ቆይተው ወደ ዞኑ ከተመለሱና ከነርሱም መካከል በሀላባ ዞን በትራንስፖርት ሲጓዝ ተይዞ ለይቶ ማቆያ ውስጥ የሚገኘው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ከተረጋገጠው ግለሰብ ጋር የቀጥታ ግንኙነት የነበረው ነው።
- በዞኑ በኮሮና ቫይረስ መያዙ ከተረጋገጠው ግለሰብ ጋር በቀጥታም ሆነ በሌላ መንገድ ግንኙነት የነበራቸው 9/ዘጠኝ/ ሰዎች በመለየት በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ወደተዘጋጀው ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ተደርገዋል።
- በአጠቃለይ በሀዲያ ዞን 51 ሰዎች በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia