TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.08K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ADDISABABA

የፐብሊክ ሰርቪስ ድርጅት ከረቡዕ ጀምሮ ተሳፋሪዎች የአፍ መሸፈኛ ጭንብል በአስገዳጅነት እንዲጠቀሙ ሊደርግ መሆኑን አስታውቋል።

ከረቡዕ ጀምሮ የአፍ መሸፈኛ ጭምብል የማይጠቀሙ ተሳፋሪዎችን እንደማይጭንም ገልጿል።

በተጨማሪ የትራንስፖርት እጥረትን ለመፍታት የመጫን አቅምን ከአስገዳጅ የአፍ መሸፈኛ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ወደ 43 የሚያድግ ይሆናል ተብሏል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በክልል ደረጃ ምርጫ ለማካሄድ ወሰነ!

የህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ከትግራይ ህዝብና ለትግራይ ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ሙሉ እውቅና ከሚሰጡ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር በመሆን ክልላዊ ምርጫን ጨምሮ የህዝቡን መብት ከትርምስ ለመታደግ የሚያስችሉ ሥራዎችን በክልል ደረጃ ለማድረግ ዝግጅት እንዲደረግ መወሰኑን አሳውቋል፡፡

የህወሃት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ይህ እንቅስቃሴ የፀረ ኮረና (ኮቪድ-19) ዘመቻዎችን እንዲሁም ተቀባይነት ያላቸውን ህገ-መንግስታዊ መርሆዎችን ባሟላ መልኩ የሚፈፀም ይሆናልም ብሏል።

ከላይ ያለውን ውሳኔ ጨምሮ ሌሎች በህወሓት የማእከላይ ኮሚቴ የተላለፉ ውሳኔዎችን ይህን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማንበብ ትችላላችሁ https://telegra.ph/TPLF-05-04

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ወቅታዊ የሀገሪቱን የፖለቲካ ሁኔታ አስመልክቶ ለTIKVAH-ETH የላከው ጋዜጣዊ መግለጫ!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

የኢትዮጵያና የአጎራባች ሀገራት የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወቅታዊ መረጃ ፦

- ጅቡቲ በቫይረሱ የተያዙ 1,116፣ ሞት 2፣ ያገገሙ 713

- ኬንያ በቫይረሱ የተያዙ 490፣ ሞት 24፣ ያገገሙ 173

- ሶማሊያ በቫይረሱ የተያዙ 756፣ ሞት 35፣ ያገገሙ 61

- ሱዳን በቫይረሱ የተያዙ 678፣ ሞት 41፣ ያገገሙ 61

- ኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ 140፣ ሞት 3፣ ያገገሙ 75

- ደቡብ ሱዳን በቫይረሱ የተያዙ 49፣ ሞት 0፣ ያገገሙ 2

- ኤርትራ በቫይረሱ የተያዙ 39 ፣ ሞት 0 ፣ ያገገሙ 26

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የቲክቫህ ኢትዮጵያ (Tikvah-Ethiopia) #ቤተሰብ አባላት መረጃዎችን የሚለዋወጡባቸው ትክክለኛ ገፆች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ብቻ ናቸው ፦

- @TIKVAHETHMAGAZINE (ከኮቪድ-19 ውጭ ያሉ ወቅታዊ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ መረጃዎች እየተሰባሰቡ የሚቀመጡበት) ከ 187,000 በላይ የቤተሰብ አባላት ያሉበት!

- @TIKVAHETHSPORT (ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መረጃዎች እየተሰባሰቡ የሚቀመጡበት) ከ 72,000 በላይ የቤተሰብ አባላት ያሉበት!

- @tikvahethAFAANOROMOO (በአፋን ኦሮሞ ወቅታዊ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ መረጃዎች እየተሰባሰቡ የሚቀመጡበት) ከ 9,000 በላይ የቤተሰብ አባላት ያሉበት!

ቲክቫህ በፌስቡክ፣ በኢንስታግራም፣ በትዊተር እና ዩትዩብ ምንም አይነት ገፆች የሉትም!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NewsAlert

በዛሬው ዕለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀጣይ የሚካሄደውን ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ የተቀመጡ ሦስት አንቀፆች ህገመንግስታዊ ትርጓሜ እንዲሰጣቸው በ25 ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል።

ምክር ቤቱ የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በህመንግስቱ አንቀፅ 83 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ምርጫውን መራዘም በተመለከተ ትርጉም የሚያስፈልጋቸውን አንቀፆች በአንድ ወር ወስጥ እንዲተረጉም ነው የወሰነው፡፡

የህግ፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምርጫን በተመለከተ የተቀመጡ ሶስት አንቀጾች ላይ የህገ መንግስት ትርጓሜ እንዲሰጥ የውሳኔ ሀሳብ ማቅረቡን አስታውቀዋል።

የውሳኔ ሀሳቡ የህገ መንግስቱ አንቀፅ 54/1 አንቀፅ 58/3 እና አንቀፅ 93 ከህገ መንግስት አላማ እና ግቦች እንዲሁም መሰረታዊ መርሆች ጋር ለማስተሳሰር ትርጉም እንዲሰጥባቸው የሚል ህገ መንግስታዊ የመፍትሄ ሀሳብ ነው ያቀረበው።

#HPR #EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ፦

- በኒው ዚላንድ ለሁለተኛ ቀን በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ዜጋ አልተገኘም ተብሏል። ኒው ዚላንድ ጥላ የነበረውን ጥብቅ የእንቅስቃሴ ገደብም እያላላች ትገኛለች - #BBC

- በቻይና ባለፉት 24 ሰዓት 1 ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙን ሪፖርት አድርጋለች። በሌላ በኩል በሀገሪቱ ለስምንተኛ ተከታታይ ቀን ሞት አልተመዘገበም።

- በአሜሪካ ባለፉት 24 ሰዓታት ከኮቪድ-19 ጋር የተያያዘ ዝቅተኛው የሞት መጠን ተመዝግቧል፤ የሟቾች ቁጥር 1015 ሲሆን ይህም ከአንድ ወር በኋላ ዝቅተኛው ነው - #BBC

- ባለፉት 24 ሰዓት በደቡብ ኮሪያ 3 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ ሁሉም ከውጭ ሀገር የገቡ ናቸው (በሀገር ውስጥ ቫይረሱ ሳይገኝ ሁለት ቀን ሆኖታል)

- ካምቦዲያ ባለፉት 3 ሳምንታት በኮቪድ-19 የተያዘ ሰው ስለመኖሩ ሪፖርት አላደረገችም። ካምቦዲያ በቫይረሱ ከተያዙ 122 ሰዎች 120ዎቹ በፍጥነት እንዲያገግሙ በመርዳት አመርቂ ውጤት አስመዝግባለች- #BBC

- ደቡብ አፍሪካ በትላንትናው ዕለት ብቻ 437 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ሪፖርት አድርጋለች። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 7,220 ደርሷል።

- ናይጄሪያ በአንድ ቀን ከፍተኛ ነው የተባለለትን በኮቪድ-19 የተያዘ የሰው ቁጥር ሪፖርት አድርጋለች፤ ባለፉት 24 ሰዓት 245 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፤ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 2,802 ደርሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

ዛሬ የዓለም የእጅ ንጽህና ቀን የሚከበርበት እለት ነው!

የዓለም የእጅ ንጽህና ቀንን በማስመልከት የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ተከታዩን መልዕክት አስተላልፈዋል ፦

''ዛሬ የዓለም የእጅ ንጽህና ቀንን ስናከብር ኢንፌክሽኖችን ለመከላከል እና ኮሮና ቫይረስን (ኮቪድ-19) ጨምሮ ጀርሞች እንዳይሰራጩ ለመከላከል የእጅ ንጽህናን መጠበቅ ውጤታማ መንገድ መሆኑን ተገንዝበን የባህሪ ለውጥ በማምጣት እራሳችንን እና ሌሎችን እንጠብቅ።''

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ባስመዘገብነው ድል ሁላችንም ልንኮራ ይገባል" - ጃሲንዳ አርደን

ኒው ዚላንድ ለሁለተኛ ቀን በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የተያዘ ዜጋ እንዳልተገኘ አሳውቃለች። ሀገሪቷ ጥላ የነበረውን ጥብቅ የእንቅስቃሴ ገደብም እያላላች ትገኛለች። ጠቅላይ ሚንስትር ጃኪንዳ አርደረን 'ባስመዘገብነው ድል ሁላችንም ልንኮራ ይገባል' ካሉ በኋላ የአገሪቱ ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል - #ቢቢሲ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 5 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!

ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 1,047 ላቦራቶሪ ምርመራ አምስት (5) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር መቶ አርባ አምስት (145) ደርሷል።

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦

ታማሚ 1 - የ75 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ #የሌላቸው፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት በመጣራት ላይ ያለ (በጤና ተቋም ተኝተው ከሚታከሙ ህሙማን ከተወሰደ ናሙና የተገኘ)

ታማሚ 2 - የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ የመኖሪያ ቦታ አፋር ፤ ከጅቡቲ የተመለሰና በአፋር አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።

ታማሚ 3 - የ22 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ የመኖሪያ ቦታ አፋር ፤ ከጅቡቲ የተመለሰና በአፋር አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።

ታማሚ 4 - የ8 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የላትም፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #ያላት

ታማሚ 5 - የ19 ዓመት ኢትዮጵያዊት የመኖሪያ ቦታ ኦሮሚያ #ባቱ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የላትም፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #ያላት

ተጨማሪ መረጃ ፦

በትላንትናው ዕለት 16 ሰዎች (15 ከአዲስ አበባ እና 1 ከአማራ ክልል) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ዘጠና አንድ (91) ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥር 4 ደርሷል!

በዛሬው መግለጫ ላይ የተጠቀሱት የ75 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት በተጓዳኝ ህመም በሆስፒታል ውስጥ ተኝተው ሲታከሙ የነበሩ ሲሆን በገጠማቸው የመተንፈስ ችግር ምክንያት በኮሮና ቫይረስ በሽታ ተጠርጥረው ምርመራ ናሙና ከተወሰደ በኃላ በምርመራ ውጤቱ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ከመረጋገጡ በፊት ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል።

#MoH #EPHI #DrLiaTadesse
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ ፦

• አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ - 25,135
• በ24 ሰዓት የተከናወነ ላብራቶሪ ምርመራ - 1,047
• ዛሬ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ - 5
• በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ - 48
• በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ - 0
• አዲስ ያገገሙ - 16
• አጠቃላይ ያገገሙ - 91
• በበሽታው ህይወታቸው ያለፈ - 4
• ወደሀገራቸው የተመለሱ - 2
• እስካሁን በበሽታው የተያዙ - 145

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#MutahiKagwe

በኬንያ በአንድ ቀን 45 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ!

በኬንያ ባለፉት 24 ሰዓት 1,077 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 45 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 535 ደርሷል።

በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት 9 ተጨማሪ ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 182 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrEbbaAbate

ከሰሞኑን 'የጊኒ ዎርም በሽታ' በተከሰተባቸው የጋምቤላ ክልል ቀበሌዎች ከ1 ሺህ 400 በላይ አባዎራዎችን ተደራሽ ያደረገ የቤት ለቤት ቅኝት መካሄዱን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኤባ አባተ ተናግረዋል ፤ የበሽታውን ምልክት በማሳየት የተጠረጠሩ 91 ሰዎች ደግሞ ለይቶ ማቆያ ማዕከል መግባታቸውን ጨምረው ገልፀዋል - #ENA

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጅቡቲ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች 1,120 ደርሰዋል!

በጅቡቲ ባለፉት 24 ሰዓት 156 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 4 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 1,120 ደርሰዋል።

በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት ተጨማሪ 32 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 745 መድረሳቸው በ24 ሰዓቱ ሪፖርት ተገልጿል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLoiceAchiengOmbajo

የኬንያ ተመራማሪዎች ለኮሮና ቫይረስ መድሃኒት ይሆናሉ ተብለው የሚገመቱ ሶስት መድሃኒቶች የክሊኒካል ሙከራ እስከሚደረግባቸው እየጠበቁ እንደሆነ ተገልጿል።

ተመራማሪዎቹ ሙከራ እስከሚደረግባቸው የሚጠብቋቸው መድሃኒቶች ኢቦላን ለማከም የሚውለው ሬምደስቪር፣ የወባ መድሃኒት እና ከኤች አይ ቪ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ኢንፌክሽኖችን ለማከም የሚውለው ሊፖናቪር ናቸው።

ዋና ተመራማሪዋ ዶ/ር ሎይስ አቺንግ ኦምባጆ እንደገለጹት ሙከራዎቹ የሚደረጉት ዓለማ አቀፍ ስርዓቶችን ተከትሎ ነው። የምርምር ስራውን ማን በገንዘብ እየደገፈው እንደሆን ግን የተባለ ነገር የለም።

በተመራማሪዋ መረጃ መሰረት የአገሪቱን የመድሃኒቶች ቦርድ እንዲሁም የብሄራዊ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ካውንስል ይሁንታ እስከሚያገኙ እየጠበቁ ነው - #BBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሱዳን ተጨማሪ 100 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸዉ ተረጋገጠ!

(በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ)

የሱዳን ጤና ሚንስቴር ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ ተጨማሪ 100 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 9 ሰዎች በተደረገላቸዉ ህክምና ማገገማቸዉን ገልጿል።

ከካርቱም ግዛት ብቻ 86 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 8 ሰዎች ከሰሜናዊ ኮርዶፋ እንደሁም የተቀሩት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል መያዛቸዉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በአጠቃላይ በሀገሪቱ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 778 የደረሰ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ 45 ሰዎች ህይወታቸዉ ሲያልፍ 70 ሰዎች ማገገማቸዉ ተገልጿል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሱማሊያ በአንድ ቀን 79 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ!

ባለፉት 24 ሰዓት በሱማሊያ ተጨማሪ 79 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 835 ደርሷል።

በሌላ በኩል አስራ አራት (14) ተጨማሪ ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 75 ደርሷል።

በተጨማሪ ባለፉት 24 ሰዓት የሶስት (3) ሰው ህይወት ማለፉ ሪፖርት ተደርጓል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር ሰላሳ አምስት (35) ደርሷል።

በተጨማሪ በሀገሪቱ የሟቾች ቁጥር ወደ 38 ከፍ ብሏል ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ የሶስት (3) ሰዎች ህይወት ማለፉ ሪፖርት ተደርጓል፤

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና!

የአዳማ ጀነራል ሆስፒታል እና የህክምና ኮሌጅ ዋና ሥራ አስፈፃሚና ባለቤት የሆኑት አቶ ከቢር ሁሴን ዋቆ ዛሬ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል፡፡

አቶ ከቢር ሁሴን ዋቆ ብዙዎች በማይደፍሩት የጤና ዘርፍ ላይ ኃብታቸውን አውጥተው በምስራቅ አፍሪካ ትልቅ የሚባለውን ሆስፒታል ሰርተው ለህብረተሰቡ እስካሁን ግልጋሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia