TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ስካይ ላይት ሆቴል በተለያዩ ከተሞች ሊገነባ ነው...

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስካይላይት ሆቴል ቅርንጫፎችን በአገሪቷ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ለማስገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን አሰታውቋል።

ሆቴሎቹ በዳሎል ፣ በኤርታሌ ፣ በባሌ ተራሮች፣ በራስ ዳሽን፣ በአርባ ምንጭና በሌሎች የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች እንደሚገነቡ ነው የተሰማው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#NewsAlert

የኮሮና ቫይረስ ሊባኖስ መግባቱ ተረጋገጠ!

የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ በሀገሪቱ የመጀመሪያ የኮሮና ቫይረስ [COVID19] ተጠቂ መገኘቱን አረጋግጧል። ከኢራን ወደ ቤሩት ገብታለች የተባለች የ45 ዓመት የሊባኖስ ዜግነት ያላት ሴት ቫይረሱ እንደሚገኝባት ተረጋግጧል። ሌሎች ሁለት በቫይረሱ ሳይጠቁ አይቀሩም የተባሉ ሰዎች ላይ ደግሞ ምርመራ እየተደረገባቸው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"በእኔ ደረጃ በአደባባይ የሚሰደብ ጠ/ሚ የለም" - ዶ/ር አብይ

ከሰሞኑን በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ከህዝብ ጋር ውይይት ያደርጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ተከታዩን ሲናገሩ ተደምጠዋል፦

አሁን ወጥቶ ሚሳደበውን ወጥቶ ሚራገመውን ሁሉ ሰድበን፣ ሁሉ አስረን እንችለዋለን? በኢትዮጵያ ውስጥ እንደምታውቁት በኔ ደረጃ በአደባባይ ሚሰደብ ጠቅላይ ሚኒስትር የለም።

ድሮ ተሳድባችሁ ሳይሆን፤ ልትሳደቡ አስባችኃል ተብላችሁ ትታሰሩ ነበር። አስባችኃል ያልኩት ቀልድ አይደለም፤ 'ድምፃችን ይሰማ' እኮ እንዲህ አስባችኃል ተብለው የታሰሩ ናቸው።

ህገ መንግስት ይከበር፣ የሃይማኖት እኩልነት ይከበር፣ ድምፃችን ይሰማ ሲሉ፤ አይ ይሄን አይደለም ያላችሁት ያሰባችሁት ሌላ ነገር አለ ተብለው ነው የታሰሩት። እንጂማ ህገ መንግስት ይከብር እንዴት ሰው ያሳስራል።

አሁን ደግሞ ህገ መንግስት ይከበር፣ ሙስሊም እውቅና ያግኝ፣ እስላሚክ ባንክ ይኑር፣ መጅሊሱ ተቋም ይሁን፤ ተቋም ይሁን ማለት ምን እንደሆነ አይገባችሁም፤ ለምሳሌ ሳዑዲ በህግ እውቅና ካልሰጠን በስተቀር እስላሚክ ሴንተር መፈራረም አይችልም ከመጅሊስ ጋር፤ አሁን እውቅና አግኝተን ወር ሳይሞላ 80 እና 90 ሚሊዮን ዶላር እያመጣን ነው እኮ።

ይሄን የሚየውቁ ሰዎች እኛን መልሰው የሙስሊም ጠላይ ይላሉ። ሚናገር ሰው ሚያጥላላ ሰው ካለ ትክክል አይደለም። እንኳን መስጅድ የአንድ ሰው ደሳሳ ጎጆ መቃጠል የለበትም።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#Election2012

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ባዘጋጀው እና የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ተወካይ ወ/ሮ ሄተር ፈላይን በተገኙበት በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ባለው የለውጥ እንቅስቃሴ እና ምርጫ 2012 አስመልክቶ ውይይት ተካሂዷል፡፡

አዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በተካሄደው እና ዓላማው በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ የፖለቲካ እና የምርጫ ዝግጅት ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መረጃ ለመሰብሰብ እንደሆነ በተገለጸው በዚሁ የውይይት መድረክ፣ የምርጫውን የግዜ ሰሌዳ፣ በተፎካካሪ ፓርቲዎች እና በገዥው ፓርቲ መካከል ያለው ግንኙነት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያጋጥሟቸው ችግሮች፣ የምርጫ ቦርድ ዝግጅት እና አቅም፣ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል፡፡

በውይይቱ የተገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች አጠቃላይ የለውጥ ሂደቱን እና ምርጫ 2012 አስመልክቶ ያጋጠሟቸውን ችግሮች እንዲሁም ገዥው ፓርቲ በተፎካካሪ ፓርቲዎች ላይ በማድረስ ላይ ነው ያሏቸውን ልዩ ልዩ ጫናዎች ለኤምባሲው ተወካዮች ገልጸዋል፡፡ የመንግስት ሀብትን እና ሚዲያን በብቸኝነት መጠቀም ፓርቲዎቹ በገዠው ፓርቲ ላይ ካነሷቸው ችግሮች መካከል ይገኙበታል፡፡

የፓርቲዎቹ ተወካዮች የአሜሪካ መንግስት ከሁሉም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በእኩል ርቀት ላይ ሊቆም እና በተለይ ለገዢው ፓርቲ የተለየ ድጋፍ ማድረግ የፖለቲካ ሜዳውን እና በዚህ አመት በሚካሄደው ምርጫ ውጤት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚኖረው ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡

More https://telegra.ph/ETH-02-21-2

#FreedomandEqualityParty

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#Election2012

በዛሬው የሂልተን ሆቴል የውይይት መድረክ ላይ የተሳተፉ ፓርቲዎች፦

1. ኦጋዴን ብሄራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ)
2. አማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን)
3. ኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
4. አረና ትግራይ ለዴሞክራሲ እና ሉአላዊነት (አረና)
5. ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)
6. የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ)
7. ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ)

ምንጭ፦ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የሜቴክና አብን አመራሮች ከእስር ከሚለቀቁት ውስጥ ናቸው!

ነገ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአንባቢያን የምትቀርበው "ሲራራ" ጋዜጣ በፊት ለፊት ገጿ ላይ ተከታዩን መረጃ ይዛለች፦

ከሰሞኑን ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ ከለውጡ በኃላ በተለያዩ አካባቢዎች በወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩትን የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ሲባል ጉዳያቸው በአግባቡ በህግ ታይቶ እንዲለቀቁ አቅጣጫ መቀመጡን መግለፃቸው አይዘነጋም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ ይህን ብለው የነበረው ከትግራይ ተወላጅ የብልፅግና ፓርቲ አባላት ጋር የካቲት 10 ቀን 2012 ዓ/ም ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው።

ነገ ለአንባቢያን የምትቀርበው 'ሲራራ' ጋዜጣ ደግሞ ከእስር ከሚፈቱት መካከል የብረታ ብረትና ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን የስራ ኃላፊዎች፣ ከሰኔ 15 ክስተት ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙት የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አመራሮችና ሌሎች እስረኞች እንዲሁም በአጣዬና ከሚሴ በተፈጠሩ ግጭቶች ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎች እንደሚገኙበት ከምጮቼ ሰምቻለው ብላለች።

#ሲራራጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በተለያዩ መንገዶች ምነው? ምን ሆናችሁ? እያላችሁ ስትጠይቁን፣ መቼም ጠያቂ አያሳጣን እያልን በልባችን መደሰታችንን ልንደብቅ አንችልም።

ጠፋ ብሎ የተመለሰን ሰው "እጅ ከምን?" ማለት አይቀርምና እኛም ባዶ እጃችንን አልተመለስንም። ከተወሰነ የአቀራረብ ለውጥና ከአዳዲስ ነገሮችን ይይዘናል።

ዙር ሰላሳ ዲጂታል መፅሔት የካቲት ወር 12 እትም
መልካም ንባብ!
@AccessAddis
ዙር30-ቅጽ2-ቁጥር 2.pdf
2.3 MB
ዙር30-ቅጽ2-ቁጥር 2
ዙር ሰላሳ!!
የካቲት ወር አስራ ሁለተኛ እትም!!
ዲጅታል መፅሔት!!
በሐገርኛ ቋንቋ
@AccessAddis
@AccessAddis
Forwarded from TIKVAH-SPORT
የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የወሩ ምርጥ አሰልጣኝ !

ቲኪቫህ ስፖርት በየወሩ ወደ እናንተ በሚያደርሰው የወሩ እጩዎች በዚህ ወር የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኝ ሰርዳን ዝቪጂኖቭ አሸናፊ መሆን ችለዋል ::

ሰርዳን ዚቪጂኖቭ ማግኘት ከሚገባቸው 21 ነጥቦች 14 ነጥቦች ሲያገኙ ካደረጉት ሰባት ጨዋታዎች በአንዱ ብቻ ሽንፈትን አስተናግደዋል ::

@tikvahethsport @kidusyoftahe @GoitomH
Forwarded from TIKVAH-SPORT
የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የወሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች !

ቲኪቫህ ስፖርት በየወሩ ወደ እናንተ በሚያደርሰው የወሩ እጩዎች በዚህ ወር የወልቂጤ ከተማው ጫላ ተሺታ አሸናፊ መሆን ችለዋል ::

ጫላ ተሺታ ባለፉት ጨዋታዎች ላይ በሶስት ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎን ማድረግ ሲችል የቲኪቫህ ቤተሰቦች አብላጫ ድምፅ በማግኘት አሸናፊ ሆኗል ::

@tikvahethsport @kidusyoftahe @GoitomH
#Election2012

የትግራይ ዴሞክራቲክ ፓርቲ /ትዴፓ/ በመጪው አገራዊ ምርጫ በትግራይ ክልል በዴሞከራሲያዊ መንገድ መወዳደር የሚያስችል እንቅስቃሴ ለማድረግ ተቸግሬያለሁ አለ፡፡

የፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር አረጋዊ በርሄ እንደገለፁት ፓርቲያቸው በመጪው አገራዊ ምርጫ በክልል ደረጃ ተወዳድሮ ለማሸነፍ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። ነገር ግን በአካባቢው ከሚንቀሳቀሰው ህወሃት የተለያዩ ችግሮች እየገጠማቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ፓርቲው በክልሉ በመቀሌ ብቻ ቅርንጫፍ መክፈቱን የገለጹት ዶክተር አረጋዊ ፤ በአብይአዲ፣ በሽሬና በአድዋ ቅርንጫፎች ለመክፈት ሙከራ ማድረጉንም ጠቅሰዋል።

ይሁንና በትግራይ ክልል ነጻና ፍትሃዊ የምርጫ እንቅስቃሴ ለማድረግ መቸገሩንና አባላቱም ለእስራት፣ ለድብደባና ለእንግልት እየተዳረጉ መሆኑን ጠቁመዋል። “ይህ ባለበትና ምርጫ ቦርድ ባለሙያዎች ባልመደበበት ሁኔታ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ ምርጫ ለማከናወን ማቀዱ ተገቢ አይደለም” ነው ያሉት።

ችግሩን በተመለከተ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ለምርጫ ቦርድና ለጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በደብዳቤ በማሳወቅ ምላሽ እየተጠባበቁ መሆኑንም ዶክተር አረጋዊ አስረድተዋል።

#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል!

ጅማ ዩኒቨርስቲ በቅድመና በድህረ ምረቃ ዘርፎች ያስተማራቸውን 3 ሺህ 139 ተማሪዎች ዛሬ እያስመረቀ ነው። ከእነዚህ ምሩቃን ውስጥም 237 የህክምና ዶክተሮች፣ 27 የጥርስ ህክምና ዶክተሮች 8ቱ ደግሞ የሶስተኛ ድግሪ ተመራቂዎች ናቸው፡፡ ከተመራቂዎች መካከልም 13ቱ ከሶማሊላንድና ከሩዋንዳ የመጡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ለኮሮና ቫይረስ- COVID-19 የቅድመ መከላከልና ጥንቃቄ ስራዎች የሚያግዙ የተለያዩ የህክምና ግብዓቶች ከአለም ጤና ድርጅት በድጋፍ ማግኘቱን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የኮሮና ቫይረስ- COVID-19 የቅድመ መከላከልና ጥንቃቄ እንዲሁም የድንገተኛ አደጋ ምላሽ ስራዎች የሚያግዙ የተለያዩ የህክምና ግብዓቶች ከአለም ጤና ድርጅት ድጋፍ የተደረገ ሲሆን ግብዓቶቹም በተለይ ለጤና ባለሙያዎች የስራ ላይ የደህንነት መጠበቂያ ሁነው ያገልግላሉ ተብሏል፡፡ ግብዓቶቹም አጠቃላይ ወጪ ከ 43 ሺህ ዶላር በላይ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በኮሮና ቫይረስ - COVID-19 ዙርያ የቅድመ መከላከልና ጥንቃቄ እንዲሁም የድንገተኛ አደጋ ምላሽ ስራዎች እየተሰራ እንደሆነና አስካሁንም በኮሮና ቫይረስ #COVID19 ምልክቱ ታይቶበት በለይቶ ማቆያ ውስጥ የሚገኝ አንድም ተጠርጣሪ የለም፡፡

ምንጭ፦ ጤና ሚኒስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦቻችን ለኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ኢንፌክሽን የሚያጋልጠንን አጋጣሚ እንቀንስ ዘንድ ጤና ሚኒስቴር እጃችንን በሳሙና እና በንፁህ ውሃ በሚገባ እንድንታጠብ መልዕክቱን አስተላልፎልናል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NEW

በፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ አዲስ ለተቀጠራችሁ በሙሉ፦

የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት የቅድመ ስራ ስልጠና ስለሚሰጥ በተጠቀሰው የማሰልጠኛ አድራሻዎች ላይ ሰኞ ከጥዋቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ተገኝታችሁ ስልጠናውን በጥብቅ ድሲፕሊን እንድትከታተሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ አሳውቋል።

የማሰልጠኛ አድራሻዎች : https://telegra.ph/ETH-02-22

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NEW

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በ 0 አመት አዲስ ቅጥር የ2010 እና 2011 ዓ.ም በተለያዩ የመንግስትና የግል ዩንቨርሲቲ በመጀመሪያ ድግሪ የተመረቃችሁ የተወዳደራችሁ እና ፈተና ከወሰዳችሁ ውስጥ በኮድ አፃፃፍ ስህተት እና በሌሎችም ቅሬታ ያቀረቡና ያላቀረቡትንም ጨምሮ ለየካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም ምላሽ እንደምንሰጥ በማስታወቂያ መለጠፋችን ይታወቃል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

1. በኮድ (ID) ስህተት ምክንያት ውጤታቸው የተሰረዘ ቅሬታ ያቀረቡም ሆነ ያላቀረቡ በሙሉ የማጣራት ስራ የተሰራ በመሆኑ ፤

2. ከማለፊያ ነጥብ በላይ የሆኑ waiting በተጠባባቂ የሚመደቡ የሚል የሚያሳይ መሆኑ፤

3. ከማለፊያ ነጥብ በታች የሆኑ Failed የሚል የሚያሳይ መሆኑ፤

More https://telegra.ph/ETH-02-22-2

[የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

ፕ/ሩን በሚመለከት የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው!

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት 'ህወሓት ወንጀል ፈጥሮላቸው የፍርድ ቤት ክስ እና ማዘዣ ወጣባቸው' በሚል በፌስቡክ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጀ ሀሰተኛ ነው። መረጀው የፈጠራ ወሬ እንደሆንም ሰምተናል። ፕሮፌሰር ክንደያም መረጃውን 'ውሸት' ሲሉ ገልፀውታል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የድጋፍ ሰልፎች ዛሬም ቀጥለዋል...

ዛሬም የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድን የለውጥ አመራር የሚደግፉ ሰልፎች እየተካሄዱ እንደሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል። ዛሬ የድጋፍ ሰልፍ እየተደረገ ከሚገኝባቸው ከተሞች መካከል የቡሌ ሆራ ከተማ አንደኛዋ ስትሆን በሰልፉ ላይ የተሳተፉ አካላት በጥላቻ እና በስድብ ሀገር መገንባት እንደማይቻል መልዕክት እያስተላለፉ ይገኛሉ።

በሌላ በኩል፦

ዱከም በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ ስራ የሚደግፍ ሰላማዊ ስልፍ እያስተናገደች ነው። ሰልፈኞቹ “በሀገሪቱ እየተከናወነ ያለውን የለውጥ ስራ እንደግፋለን”፣ “ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ አመራር ጎን ነን”  የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮችን በማሰማት ነው የድጋፍ ሰልፉን በማካሄድ ላይ የሚገኙት። በከተማዋ እና በዙሪያ የሚገኙ ነዋሪዎችም በሰልፉ ላይ በመሳተፍ ላይ ናቸው ተብሏል።

#TikvahFamily #FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia