የጥላቻ ንግግር...
በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተበራከተ የመጣው የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ በዜጎች ደህንነት ላይ ስጋት ደቅኗል። በቅርቡም በአንዳንድ አካባቢዎች የዜጎች መፈናቀል፣ የንብረት ውድመት፣ ባስ ሲልም የሰው ሕይወት እስከመጥፋት ያደረሰ አደጋ ሲከሰት ተስተውሏል።
እንደ አውሮጳዊያኑ አቆጣጠር 1994 በሩዋንዳ፤ በ20ኛ ክፍለ ዘመን አጋማሽ በጀርመንና በአውሮጳ የደረሰው አሰቃቂ የዜጎች እልቂት የጥላቻ ንግግር በጊዜ ካልተገታ የሚያመጣው ጥፋት ከባድ መሆኑን አመላካች ነው።
ይህን አይነቱ ችግር በኢትዮጵያ እንዳይከሰት ለመከላከል መንግሥት የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ አዋጅ ለማፅደቅ በሂደት ላይ ይገኛል።
ረቂቅ አዋጁ ዜጎች ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን ሲጠቀሙ ግጭት ወይም ሁከት የሚቀሰቅስ፣ ብሄር፣ ኃይማኖት፣ ዘር፣ ጾታ፣ አካል ጉዳተኝነት፣ ግለሰብ ወይንም ቡድኖች ላይ ጥላቻ የሚያስነሱ ንግግሮችን መጠቀምን ይከለክላል። የተቀመጠውን ክልከላ ተላልፈው የተገኙ ዜጎች እንደ ጥፋቱ ደረጃ ከአንድ እስከ አምስት ዓመት እስር ሊፈረድባቸው፤ ከ50 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ሊጣልባቸው እንደሚችልም ይደነግጋል።
More https://telegra.ph/ENA-02-01
[ኢዜአ]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተበራከተ የመጣው የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ በዜጎች ደህንነት ላይ ስጋት ደቅኗል። በቅርቡም በአንዳንድ አካባቢዎች የዜጎች መፈናቀል፣ የንብረት ውድመት፣ ባስ ሲልም የሰው ሕይወት እስከመጥፋት ያደረሰ አደጋ ሲከሰት ተስተውሏል።
እንደ አውሮጳዊያኑ አቆጣጠር 1994 በሩዋንዳ፤ በ20ኛ ክፍለ ዘመን አጋማሽ በጀርመንና በአውሮጳ የደረሰው አሰቃቂ የዜጎች እልቂት የጥላቻ ንግግር በጊዜ ካልተገታ የሚያመጣው ጥፋት ከባድ መሆኑን አመላካች ነው።
ይህን አይነቱ ችግር በኢትዮጵያ እንዳይከሰት ለመከላከል መንግሥት የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ አዋጅ ለማፅደቅ በሂደት ላይ ይገኛል።
ረቂቅ አዋጁ ዜጎች ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን ሲጠቀሙ ግጭት ወይም ሁከት የሚቀሰቅስ፣ ብሄር፣ ኃይማኖት፣ ዘር፣ ጾታ፣ አካል ጉዳተኝነት፣ ግለሰብ ወይንም ቡድኖች ላይ ጥላቻ የሚያስነሱ ንግግሮችን መጠቀምን ይከለክላል። የተቀመጠውን ክልከላ ተላልፈው የተገኙ ዜጎች እንደ ጥፋቱ ደረጃ ከአንድ እስከ አምስት ዓመት እስር ሊፈረድባቸው፤ ከ50 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ሊጣልባቸው እንደሚችልም ይደነግጋል።
More https://telegra.ph/ENA-02-01
[ኢዜአ]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የእንቦጭ አረም ወደ ጫሞ ሃይል ተስፋፍቷል...
በጋሞ ዞን በአባያ ሀይቅ ላይ ተከስቶ የነበረው የእንቦጭ አረም ወደ ጫሞ ሀይቅ በመስፋፋቱ አሳሰቢ ደረጃ መድረሱን የዞኑ አካባቢ ጥበቃና ደን ልማት ጽህፈት ቤት ገለጸ።
በጽህፈት ቤቱ የብዝሃ ህይወት ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ጋንቡራ ጋንታ እንዳሉት በጫሞ ሀይቅ ላይ ከ10 ሄክታር በላይ የሚሸፍን የውሃው ክፍል በአረሙ ተወሯል፡፡
ይህም ቀደም ሲል በአባያ ሀይቅ ላይ ከ2ሺህ ሄካታር በላይ የሸፈነው የእንቦጭ አረም በሚፈጠረው ማዕበልና ከኩልፎ ወንዝ ተፋሰስ በመታገዝ ተስፋፍቶ የመጣ መሆኑን አስረድተዋል።
[ENA]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በጋሞ ዞን በአባያ ሀይቅ ላይ ተከስቶ የነበረው የእንቦጭ አረም ወደ ጫሞ ሀይቅ በመስፋፋቱ አሳሰቢ ደረጃ መድረሱን የዞኑ አካባቢ ጥበቃና ደን ልማት ጽህፈት ቤት ገለጸ።
በጽህፈት ቤቱ የብዝሃ ህይወት ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ጋንቡራ ጋንታ እንዳሉት በጫሞ ሀይቅ ላይ ከ10 ሄክታር በላይ የሚሸፍን የውሃው ክፍል በአረሙ ተወሯል፡፡
ይህም ቀደም ሲል በአባያ ሀይቅ ላይ ከ2ሺህ ሄካታር በላይ የሸፈነው የእንቦጭ አረም በሚፈጠረው ማዕበልና ከኩልፎ ወንዝ ተፋሰስ በመታገዝ ተስፋፍቶ የመጣ መሆኑን አስረድተዋል።
[ENA]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#UPDATE
ኮሮና ቫይረስ የዓለም ስጋት መሆኑ ቀጥሎ ፊሊፒንስ ውስጥ አንድ ግለሰብ በቫይረሱ ህይወቱ ማለፏ ተረጋግጧል። ከቻይና ውጪ በቫይረሱ ሰው ሲሞት ይህ የመጀመሪያው ነው።
የ44 ዓመቱ ቻይናዊ ግለሰብ በሁቤ ግዛት በምትገኘው ዉሃን ከተባለችው ከተማ የመጣ ሲሆን ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውም በዚችው ከተማ ነበር። የዓለምአቀፉ ጤና ድርጅት እንዳስታወቀው ግለሰቡ ፊሊፒንስ ከመድረሱ በፊት በቫይረሱ ተይዞ ነበር።
[BBC]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ኮሮና ቫይረስ የዓለም ስጋት መሆኑ ቀጥሎ ፊሊፒንስ ውስጥ አንድ ግለሰብ በቫይረሱ ህይወቱ ማለፏ ተረጋግጧል። ከቻይና ውጪ በቫይረሱ ሰው ሲሞት ይህ የመጀመሪያው ነው።
የ44 ዓመቱ ቻይናዊ ግለሰብ በሁቤ ግዛት በምትገኘው ዉሃን ከተባለችው ከተማ የመጣ ሲሆን ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘውም በዚችው ከተማ ነበር። የዓለምአቀፉ ጤና ድርጅት እንዳስታወቀው ግለሰቡ ፊሊፒንስ ከመድረሱ በፊት በቫይረሱ ተይዞ ነበር።
[BBC]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የፊሊፒንስ ዜጎች እንዲረጋጉ ጥሪ ተላልፎላቸዋል...
ከቻይና ተጉዞ ፊሊፒንስ ውስጥ ህይወቱ ያለፈው ግለሰብ ከእሱ በተጨማሪ አብራው የነበረችው የ38 ዓመቷ ቻይናዊ ባለቤቱ በቫይረሱ እንደተያዘች ማረጋገጣቸውን የሀገሪቱ የጤና ኃላፊዎች አስታውቀዋል።
በፊሊፒንስ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ የሆኑት ራቢንድራ አቤያሲንግ ዜጎች እንዲረጋጉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ''ከቻይና ውጪ በቫይረሱ ሰው ሲሞት ይህ የመጀመሪያው ነው። መርሳት የሌለብን ግን ግለሰቡ በሽታውን ከቻይና ይዞት መምጣቱን ነው'' ብለዋል።
[BBC]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ከቻይና ተጉዞ ፊሊፒንስ ውስጥ ህይወቱ ያለፈው ግለሰብ ከእሱ በተጨማሪ አብራው የነበረችው የ38 ዓመቷ ቻይናዊ ባለቤቱ በቫይረሱ እንደተያዘች ማረጋገጣቸውን የሀገሪቱ የጤና ኃላፊዎች አስታውቀዋል።
በፊሊፒንስ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ የሆኑት ራቢንድራ አቤያሲንግ ዜጎች እንዲረጋጉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ''ከቻይና ውጪ በቫይረሱ ሰው ሲሞት ይህ የመጀመሪያው ነው። መርሳት የሌለብን ግን ግለሰቡ በሽታውን ከቻይና ይዞት መምጣቱን ነው'' ብለዋል።
[BBC]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#UPDATE
በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 305 ደርሷል። 14,559 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ መጠቃታቸው ተሰምቷል። #nCoV
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 305 ደርሷል። 14,559 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ መጠቃታቸው ተሰምቷል። #nCoV
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
#UPDATE
- የአሜሪካ
- የአውስትራሊያ
- የኬንያ
- የሩዋንዳ
- የማዳጋስካር
- የሞሪሸስ እና የሞሮኮ አየር መንገዶች ወደ ቻይናና ከቻይና ያደርጓቸው የነበሩትን ሁሉንም ጉዞዎች ለጊዜው አቁመዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁንም የኮሮና ቫይረስ ባስፋት ባልተስፋፋባቸው የቻይና ከተሞች ሻንጋይ፣ ቤጂንግ ፣ ጉዋንዡ፣ ቼንግዱ በከፍተኛ ጥንቃቄ በረራዬን ቀጥያለሁ ማለቱ ይታወቃል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
- የአሜሪካ
- የአውስትራሊያ
- የኬንያ
- የሩዋንዳ
- የማዳጋስካር
- የሞሪሸስ እና የሞሮኮ አየር መንገዶች ወደ ቻይናና ከቻይና ያደርጓቸው የነበሩትን ሁሉንም ጉዞዎች ለጊዜው አቁመዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁንም የኮሮና ቫይረስ ባስፋት ባልተስፋፋባቸው የቻይና ከተሞች ሻንጋይ፣ ቤጂንግ ፣ ጉዋንዡ፣ ቼንግዱ በከፍተኛ ጥንቃቄ በረራዬን ቀጥያለሁ ማለቱ ይታወቃል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
“ሴቶችን ማገት ሀገር ማገት ነው”
ሰለታገቱት ተማሪዎች በጎንደርና በሌሎች ከተሞች ሰልፍ ተካሂዷል። በደምቢዶሎ ዪንቨርስቲ ይማሩ የነበሩ እና ከሁለት ወር በፊት ወደቤት ሲመለሱ እስከአሁነ ማንነታቸው ባልታወቀ ቡድኖች ስለተጋቱት 17 የአማራ ክልል ተማሪዎች መንግስት ከእገታው እንዲያስለቅቃቸው ለማድረግ ዛሬ ጥር 24 ከጠዋት አንድ አሰአት ጀምሮ በጎንደር ፣በደብረ ታቦር ፣ በዋግኅምራ እና በሌሎች የአማራ ክልል ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ እየተደረገ ነው። ሴቶችን ማገት ሀገር ማገት ነው፣ ሴቶቻችን ይለቀቁ ፣ሴቶች ሚኒስትሮች የት አላቹ? የሚሉ መፈክሮች በሰላሚዊ ሰልፉ ላይ ታይተዋል።
ከታዳጊ ተማሪዎች አንስቶ ወጣቶች ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ አዛውንቶች እና ጎልማሶች በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ተሳትፈዋል።ከቀናት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅህፈት ቤት በተሰጠ መግለጫ የታገቱት ተማሪዎች በሕይወት እንዳሉ ቢገለፅም ለጥንቃቄ ሲባል የት እና በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ የተነገረ ነገር የለም።
[ፊደል ፓስት፣ PHOTO :AMMA]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ሰለታገቱት ተማሪዎች በጎንደርና በሌሎች ከተሞች ሰልፍ ተካሂዷል። በደምቢዶሎ ዪንቨርስቲ ይማሩ የነበሩ እና ከሁለት ወር በፊት ወደቤት ሲመለሱ እስከአሁነ ማንነታቸው ባልታወቀ ቡድኖች ስለተጋቱት 17 የአማራ ክልል ተማሪዎች መንግስት ከእገታው እንዲያስለቅቃቸው ለማድረግ ዛሬ ጥር 24 ከጠዋት አንድ አሰአት ጀምሮ በጎንደር ፣በደብረ ታቦር ፣ በዋግኅምራ እና በሌሎች የአማራ ክልል ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ እየተደረገ ነው። ሴቶችን ማገት ሀገር ማገት ነው፣ ሴቶቻችን ይለቀቁ ፣ሴቶች ሚኒስትሮች የት አላቹ? የሚሉ መፈክሮች በሰላሚዊ ሰልፉ ላይ ታይተዋል።
ከታዳጊ ተማሪዎች አንስቶ ወጣቶች ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ አዛውንቶች እና ጎልማሶች በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ተሳትፈዋል።ከቀናት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅህፈት ቤት በተሰጠ መግለጫ የታገቱት ተማሪዎች በሕይወት እንዳሉ ቢገለፅም ለጥንቃቄ ሲባል የት እና በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ የተነገረ ነገር የለም።
[ፊደል ፓስት፣ PHOTO :AMMA]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
#JawarMohammed #Election2012 የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ [ኦፌኮ] አቶ ጃዋር መሃመድ ኢትዮጵያዊ ዜግነት እንዳለው የሚያረጋግጥ ማስረጃ እንዲያቀርብ ተጠይቋል። ጥያቄው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በፃፈው ደብዳቤ መሰረት የቀረበ እንደሆነ ነው የተረጋገጠው። ኦፌኮ በጉዳዩ ላይ ምላሽ እንዲሰጥበት የደብዳቤው ኮፒ ለአቶ ጃዋር መሃመድ ልኮለታል። ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና የተናገሩት፦ "መንግስት…
#Election2012 #JawarMohammed
"አቶ ጃዋር የኢትዮጵያ ዜጋ ሆነዋል" - ጠበቃ ገመቹ ጉተማ
በታኅሳስ ወር የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስን [ኦፌኮ] መቀላቀላቸውን ያስታወቁት ጃዋር መሐመድ ረቡዕ ጥር 13/2012 ለኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና የወሳኝ ኩነት የሚጠበቅባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት የኢትዮጵያ ዜጋ መሆናቸውን ጠበቃቸው ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግረዋል።
የጃዋር መሐመድ ጠበቃ የሆኑት ገመቹ ጉተማ፤ ጃዋር በዜግነት አዋጁ የሚጠበቅባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላታቸውን እና በዚህም መሰረት ለሚመለከተው አካል ማስገባታቸውን ገልፀዋል። ‹‹በሕጉ መሰረት ዜግነትን መልሶ ለማግኘት የምንጠብቀው ምንም ዓይነት መልስ የለም። አስፈላጊ ሰነዶችን ግን አስገብተናል›› ሲሉ ተናግረዋል።
[አዲስ ማለዳ ጋዜጣ]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"አቶ ጃዋር የኢትዮጵያ ዜጋ ሆነዋል" - ጠበቃ ገመቹ ጉተማ
በታኅሳስ ወር የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስን [ኦፌኮ] መቀላቀላቸውን ያስታወቁት ጃዋር መሐመድ ረቡዕ ጥር 13/2012 ለኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና የወሳኝ ኩነት የሚጠበቅባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት የኢትዮጵያ ዜጋ መሆናቸውን ጠበቃቸው ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግረዋል።
የጃዋር መሐመድ ጠበቃ የሆኑት ገመቹ ጉተማ፤ ጃዋር በዜግነት አዋጁ የሚጠበቅባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላታቸውን እና በዚህም መሰረት ለሚመለከተው አካል ማስገባታቸውን ገልፀዋል። ‹‹በሕጉ መሰረት ዜግነትን መልሶ ለማግኘት የምንጠብቀው ምንም ዓይነት መልስ የለም። አስፈላጊ ሰነዶችን ግን አስገብተናል›› ሲሉ ተናግረዋል።
[አዲስ ማለዳ ጋዜጣ]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#JawarMohammed
ትላንት አዲስ ስታንዳርድ በእንግሊዘኛ ቋንቋ መረጃዎች የሚያሰራጭ ድረ ገፁ አቶ ጃዋር መሃመድ ለኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ዜግነቱ እንዲመለስለት ያስገባባትን ሁለት ገፅ ማመልከቻ ይዞ ወጥቷል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiabot
ትላንት አዲስ ስታንዳርድ በእንግሊዘኛ ቋንቋ መረጃዎች የሚያሰራጭ ድረ ገፁ አቶ ጃዋር መሃመድ ለኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ዜግነቱ እንዲመለስለት ያስገባባትን ሁለት ገፅ ማመልከቻ ይዞ ወጥቷል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiabot
የህዳሴው ግድብ 71℅ ደርሷል ተብሏል...
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በ2015 ዓ/ም መጨረሻ ለማጠናቀቅ ግብ ተይዞ እየተሰራ ሲሆን አሁን ላይ የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ 71% ደርሷል። ይህ የተገለፀው በትላንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት ነው፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በ2015 ዓ/ም መጨረሻ ለማጠናቀቅ ግብ ተይዞ እየተሰራ ሲሆን አሁን ላይ የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ 71% ደርሷል። ይህ የተገለፀው በትላንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት ነው፡፡
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
ቲክቫህ ቤተሰቦች ቄለም ወለጋ... ከደቂቃዎች በፊት በቄለም ወለጋ አንፊሎ/ሙጊ ከተማ ቤተሰቦቻቸው የሚኖሩ የዩዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሆኑ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በስልክ ለማግኘት ችለናል። ተማሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ በወለጋ የሰው ህይወት እየጠፋ ነው፤ መንግስት ግልፅ መረጃ ለህዝብ እየሰጠ አይደለም፤ የኢተርኔት እና ስልክ መቋረጥ ከቤተሰቦቻቸው እንዲርቁ እንዳደረጋቸውም ተናግረዋል። በሙጊ ከተማ በያዝነው…
ከቲክቫህ ቤተሰብ አባላት፦
ከዚህ ቀደም በወለጋ ቤተሰቦቻቸው የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በአካባቢው ኢንተርኔት እና በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ስልክ በመቋረጡ ሳቢያ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘት እንዳልቻሉ ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ነበር።
ዛሬም በርካታ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ሰሚ አጥተናል መንግስት በአካባቢው ፈፅመዋለሁ ስለሚለው ኦፕሬሽን ግልፅ መረጃ ይስጠን በማለት እየጠየቁ ነው።
እኚሁ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መንግስት እየወሰደ ባለው እርምጃ ንፁሃን እየተጎዱ ነው፤ ይህንንም አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ቢገልፁም የትኛውም የሀገር ውስጥ ሚዳያ አይዘግብም የቤተሰቦቻችን ድምፅ ታፍኗል ብለዋል።
በመንግስት በሚወስደው እርምጃ ንፁሃን እንዳይጎዱ ስለሚደረገው ስራ በቂና ዝርዝር መረጃ መንግስት ለህዝብ ሊሰጥ ይገባል፤ ወላጆቻችን ምን ሆኑ በሚል ተማሪዎች በአግባቡ ሊማሩ አልቻሉም ሲሉ ገልፀዋል። የሚዲያዎች ዝምታና ትኩረት መንፈግም እጅግ እንዳሳዘናቸውም ተናግረዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ከዚህ ቀደም በወለጋ ቤተሰቦቻቸው የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በአካባቢው ኢንተርኔት እና በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ስልክ በመቋረጡ ሳቢያ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘት እንዳልቻሉ ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ነበር።
ዛሬም በርካታ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ሰሚ አጥተናል መንግስት በአካባቢው ፈፅመዋለሁ ስለሚለው ኦፕሬሽን ግልፅ መረጃ ይስጠን በማለት እየጠየቁ ነው።
እኚሁ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መንግስት እየወሰደ ባለው እርምጃ ንፁሃን እየተጎዱ ነው፤ ይህንንም አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ቢገልፁም የትኛውም የሀገር ውስጥ ሚዳያ አይዘግብም የቤተሰቦቻችን ድምፅ ታፍኗል ብለዋል።
በመንግስት በሚወስደው እርምጃ ንፁሃን እንዳይጎዱ ስለሚደረገው ስራ በቂና ዝርዝር መረጃ መንግስት ለህዝብ ሊሰጥ ይገባል፤ ወላጆቻችን ምን ሆኑ በሚል ተማሪዎች በአግባቡ ሊማሩ አልቻሉም ሲሉ ገልፀዋል። የሚዲያዎች ዝምታና ትኩረት መንፈግም እጅግ እንዳሳዘናቸውም ተናግረዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የምዕራብ ወለጋ የፀጥታ ስጋት...
“ሰብዓዊ መብትትን የሚጥሱ ሰዎች ላይ ለምን እርምጃ ተወሰደ? የሚል ተቃውሞ ማሰማት እጅግ አሳዛኝ ነው” - አቶ ታዬ ደንዳአ [የኦሮሚያ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ]
"የታጠቁ አካሎች እንዳሉ እናውቃለን፤ አካባቢው ላይ የፀጥታ ችግር አለ፤ ግን እነዚህ ሰዎች ላይ እና የታጠቁ ኃይሎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች በሰላማዊ መንገድ፤ ሀሳባቸውን ከኃይል በራቀ መልኩ የሚገልፁና የሚችሉ ሰዎች እነሱ ላይ ማተኮር የለበትም። ታጥቀው ችግሩን የሚፈጥሩትን ሰዎች ለይቶ ነው እርምጃ መወሰድ ያለበት። ያየናቸው እስሮች ብዙዎቹ የከተማ ሰዎች ናቸው። እንደዛም ሆኖ በወንጀል ተሳትፈው ሊሆን ይችላል ያ ማለት ግን የህግ ከለላ ሊያገኙ አይገባም ማለት አይደለም። በ48 ሰዓት ፍርድ ቤት መቅረብ አለባቸው፣ የታሰሩበት ምክንያትና የተያዙበት ምክንያት በግልፅ ሊነገራቸው ይገባል፣ ምርመራውም ተጠናዉ ቶሎ መቅረብ አለባቸው።" - አቶ ፍስሃ ተክሌ [የአምነስቲ የአፍሪካ ቀንድ ተመራማሪ]
📹9 MB [WiFi ተጠቀሙ]
[ዘገባው ከJanuary 31 የተወሰደ ነው]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
“ሰብዓዊ መብትትን የሚጥሱ ሰዎች ላይ ለምን እርምጃ ተወሰደ? የሚል ተቃውሞ ማሰማት እጅግ አሳዛኝ ነው” - አቶ ታዬ ደንዳአ [የኦሮሚያ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ]
"የታጠቁ አካሎች እንዳሉ እናውቃለን፤ አካባቢው ላይ የፀጥታ ችግር አለ፤ ግን እነዚህ ሰዎች ላይ እና የታጠቁ ኃይሎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎች በሰላማዊ መንገድ፤ ሀሳባቸውን ከኃይል በራቀ መልኩ የሚገልፁና የሚችሉ ሰዎች እነሱ ላይ ማተኮር የለበትም። ታጥቀው ችግሩን የሚፈጥሩትን ሰዎች ለይቶ ነው እርምጃ መወሰድ ያለበት። ያየናቸው እስሮች ብዙዎቹ የከተማ ሰዎች ናቸው። እንደዛም ሆኖ በወንጀል ተሳትፈው ሊሆን ይችላል ያ ማለት ግን የህግ ከለላ ሊያገኙ አይገባም ማለት አይደለም። በ48 ሰዓት ፍርድ ቤት መቅረብ አለባቸው፣ የታሰሩበት ምክንያትና የተያዙበት ምክንያት በግልፅ ሊነገራቸው ይገባል፣ ምርመራውም ተጠናዉ ቶሎ መቅረብ አለባቸው።" - አቶ ፍስሃ ተክሌ [የአምነስቲ የአፍሪካ ቀንድ ተመራማሪ]
📹9 MB [WiFi ተጠቀሙ]
[ዘገባው ከJanuary 31 የተወሰደ ነው]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"የመንግስት ጦር ሁለት የአክስቴን ልጆች ገድሏል፤ እንዳይቀበሩም ጭምር ከልክሏል" - አቶ በቀለ ገርባ [የኦፌኮ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር]
የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ በቀለ ገርባ በግል የፌስቡክ ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሑፍ የመንግስት ጦር በትላንትናው እለት በምዕራብ ወለጋ ነጆ ወርዳ በቡያ ቦሊቲ ቀበሌ የአክስቴን ልጆች ታምሩ ታደሰን እና ጆቴ ታደሰ ገድሏል፤ መግደል ብቻ አይደለም እንዳይቀበሩም ከልክሏል ሲሉ ገልፀዋል አክለውም ሁለቱም ያልታጠቁ አርሶ አደሮች ነበሩ" ብለዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ በቀለ ገርባ በግል የፌስቡክ ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሑፍ የመንግስት ጦር በትላንትናው እለት በምዕራብ ወለጋ ነጆ ወርዳ በቡያ ቦሊቲ ቀበሌ የአክስቴን ልጆች ታምሩ ታደሰን እና ጆቴ ታደሰ ገድሏል፤ መግደል ብቻ አይደለም እንዳይቀበሩም ከልክሏል ሲሉ ገልፀዋል አክለውም ሁለቱም ያልታጠቁ አርሶ አደሮች ነበሩ" ብለዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ኮሮና ቫይረስና ማህበራዊ ሚዲያ!
ኮሮና ቫይረስን በተመለከተ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የሚወሩና የሚጋሩ ሳይንሳዊ መሰረት የሌላቸው ወሬዎች ሰዎችን ጭንቀት ውስጥ እየጣሉ፣ ቻይናውያንን ደግሞ ለከፍተኛ መገለልና የዘረኝነት ስድቦች እየዳረጉ ነው ተብሏል።
ኮሮና ቫይረስን የፅዳት ኬሚካሎችን ወይም ማቅለሚያዎችን በልኩ በመውሰድ መዳን ይቻላል የሚል ብዙዎች የተመለከቱት የፌስቡክ ፖስት እና ሌሎች የዩትዩብ ቪዲዮዎችን ለአብነት አንስቷል- ብሉምበርግ። የቻይናውያንን አመጋገብና ባህል የሚነቅፉና፣ የናንተ ቫይረስ ነው፣ እዚያው በጠበላችሁ የሚሉ የዘረኝነት ፅሁፎችን በቻይና ሬስቶራንቶች ማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ላይ ተፅፈውም ታይተዋል።
ትዊተር፣ ፌስቡክና ጉግል በሚቻል መጠን የተሳሳቱ የኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ከየገፆቻቸው ላይ ለመቀነስና ሰዎችንም ተዓማኒ ወደሆኑ ገፆች ለመምራት ጥረት እያደረጉ መሆኑን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ በኩል የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአንፃራዊነት ጥሩና ፈጣን ሊባል የሚችል መረጃን በየማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻቸውና የፕሬስ መግለጫዎች እየሰጡ ይገኛሉ። ስለቫይረሱ መረጃ ለማግኘት የእነዚህን ተቋማት ፌስቡክና ትዊተር ገፆች መመልከት መልካም ነው።
[ሃሽታግ- አዲስፕላስ፣ ኤልያስ መሰረት]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ኮሮና ቫይረስን በተመለከተ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የሚወሩና የሚጋሩ ሳይንሳዊ መሰረት የሌላቸው ወሬዎች ሰዎችን ጭንቀት ውስጥ እየጣሉ፣ ቻይናውያንን ደግሞ ለከፍተኛ መገለልና የዘረኝነት ስድቦች እየዳረጉ ነው ተብሏል።
ኮሮና ቫይረስን የፅዳት ኬሚካሎችን ወይም ማቅለሚያዎችን በልኩ በመውሰድ መዳን ይቻላል የሚል ብዙዎች የተመለከቱት የፌስቡክ ፖስት እና ሌሎች የዩትዩብ ቪዲዮዎችን ለአብነት አንስቷል- ብሉምበርግ። የቻይናውያንን አመጋገብና ባህል የሚነቅፉና፣ የናንተ ቫይረስ ነው፣ እዚያው በጠበላችሁ የሚሉ የዘረኝነት ፅሁፎችን በቻይና ሬስቶራንቶች ማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ላይ ተፅፈውም ታይተዋል።
ትዊተር፣ ፌስቡክና ጉግል በሚቻል መጠን የተሳሳቱ የኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ከየገፆቻቸው ላይ ለመቀነስና ሰዎችንም ተዓማኒ ወደሆኑ ገፆች ለመምራት ጥረት እያደረጉ መሆኑን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ በኩል የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአንፃራዊነት ጥሩና ፈጣን ሊባል የሚችል መረጃን በየማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻቸውና የፕሬስ መግለጫዎች እየሰጡ ይገኛሉ። ስለቫይረሱ መረጃ ለማግኘት የእነዚህን ተቋማት ፌስቡክና ትዊተር ገፆች መመልከት መልካም ነው።
[ሃሽታግ- አዲስፕላስ፣ ኤልያስ መሰረት]
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE - የአሜሪካ - የአውስትራሊያ - የኬንያ - የሩዋንዳ - የማዳጋስካር - የሞሪሸስ እና የሞሮኮ አየር መንገዶች ወደ ቻይናና ከቻይና ያደርጓቸው የነበሩትን ሁሉንም ጉዞዎች ለጊዜው አቁመዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ? የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁንም የኮሮና ቫይረስ ባስፋት ባልተስፋፋባቸው የቻይና ከተሞች ሻንጋይ፣ ቤጂንግ ፣ ጉዋንዡ፣ ቼንግዱ በከፍተኛ ጥንቃቄ በረራዬን ቀጥያለሁ…
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና የማደርገውን በረራ አላቋረጥኩም፤ በረራውን የማደርገውም በጥንቃቄ ነው ቢልም የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ እየተመለከትን ነው። በማህበራዊ ሚዲያዎች ዞር ዞር ስንል ይህንን አስተያየት አገኘን፦
"ለቻይና እንኳን የከበደ በሽታ ግባልን ብሎ በር መክፈት ምን ይሉት ማን አለብኝነት ነው? ሞተን አላልቅ አልን ወይ? የኢትዮጲያ አየር መንገድ በረራዬን ወደ ቻይና አላቆምም ማለቱ ምንን ተስፋ አድርጎ ነው? Temperature ለክቼ አሳልፋለሁ አለ? screening ከተባለ ፣ ሲጀመር virus Incubation period ሁለት ሳምንት አለው ፣ ሰውየው ምንም ምልክት ሳያሳይ ለሁለት ሳምንት በሽታውን ለሌሎች ማስተላለፍ ይችላል። ስለዚህ ሰውየው ትኩሳት ስለማይኖረው እቺን "screening" አለፋት ማለት ነው። ነው ወይስ ጤና ጥበቃ አቋቋምኩት ያለውን ድንኳን ተስፋ አድርጎ ነው? ድንኳኑ እሺ ይሁን ግን Corona virus ለማከም በትንሹ መተንፈሻ ማሽን (mechanical ventilators) ያስፈልጋል! ኢትዮጲያ ውስጥ ያሉት በሙሉ መተንፈሻ ማሽኖች ቢቆጠሩ 100 መሙላታቸውን እንጃ። አንዴ ወደ ሀገር ውስጥ ከገባ በሽታውን ማኔጅ የምናረግበት አቅም የለንም ፣ ደሞ በዚ ላይ አኗኗራችን ለቫይረሱ መስፋፋት ምቹ ነው ፤ ኧረ ስማ በለው!!" - ዶ/ር ነፃነት መንገሻ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"ለቻይና እንኳን የከበደ በሽታ ግባልን ብሎ በር መክፈት ምን ይሉት ማን አለብኝነት ነው? ሞተን አላልቅ አልን ወይ? የኢትዮጲያ አየር መንገድ በረራዬን ወደ ቻይና አላቆምም ማለቱ ምንን ተስፋ አድርጎ ነው? Temperature ለክቼ አሳልፋለሁ አለ? screening ከተባለ ፣ ሲጀመር virus Incubation period ሁለት ሳምንት አለው ፣ ሰውየው ምንም ምልክት ሳያሳይ ለሁለት ሳምንት በሽታውን ለሌሎች ማስተላለፍ ይችላል። ስለዚህ ሰውየው ትኩሳት ስለማይኖረው እቺን "screening" አለፋት ማለት ነው። ነው ወይስ ጤና ጥበቃ አቋቋምኩት ያለውን ድንኳን ተስፋ አድርጎ ነው? ድንኳኑ እሺ ይሁን ግን Corona virus ለማከም በትንሹ መተንፈሻ ማሽን (mechanical ventilators) ያስፈልጋል! ኢትዮጲያ ውስጥ ያሉት በሙሉ መተንፈሻ ማሽኖች ቢቆጠሩ 100 መሙላታቸውን እንጃ። አንዴ ወደ ሀገር ውስጥ ከገባ በሽታውን ማኔጅ የምናረግበት አቅም የለንም ፣ ደሞ በዚ ላይ አኗኗራችን ለቫይረሱ መስፋፋት ምቹ ነው ፤ ኧረ ስማ በለው!!" - ዶ/ር ነፃነት መንገሻ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ ምን ይላሉ፦
"ይሄ አንዲት በቻይና ዉሃን ከተማ የምትሰራ ነርስ እጅ ነው። የኮሮና በሽታ ሲከሰት በሆስፒታሉ ህጻናትን የምትከታተል ባለሙያ ነበረች። ባከመች፣ በነካች፣ በወጣችና በገባች ቁጥር እጆቿን በፀረ-ጀርም (Anti-septic) ማጽ ዳትና ጓንት መቀየር ነበረባት። ታድያ ካለእረፍት የሰራችበት እጇ እንደዚህ ተላልጧል። ክብር ይገባታል። በሽታው ግን ቀላል አይደለም። ብዙ ዋጋ ያስከፍላል። ጓንት እንኳን በቅጡ የማናሟላ አገር ሆነን ሳለን በረራ አናቆምም ማለት ትልቅ ቀልድ ነው። ለሚመጣው ችግር በሙሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጠያቂነቱን እንደሚወስድ ከወዲሁ ማወቅ አለበት። የሳንባ ምች (Pneomonia) እና ቲቢ እስካሁን ብዙዎችን በሚገድሉበት አገር ኮሮና ቢገባ የሚከሰተውን እልቂት ማሰብ ይዘገንናል። #StopFlyingToChina"
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"ይሄ አንዲት በቻይና ዉሃን ከተማ የምትሰራ ነርስ እጅ ነው። የኮሮና በሽታ ሲከሰት በሆስፒታሉ ህጻናትን የምትከታተል ባለሙያ ነበረች። ባከመች፣ በነካች፣ በወጣችና በገባች ቁጥር እጆቿን በፀረ-ጀርም (Anti-septic) ማጽ ዳትና ጓንት መቀየር ነበረባት። ታድያ ካለእረፍት የሰራችበት እጇ እንደዚህ ተላልጧል። ክብር ይገባታል። በሽታው ግን ቀላል አይደለም። ብዙ ዋጋ ያስከፍላል። ጓንት እንኳን በቅጡ የማናሟላ አገር ሆነን ሳለን በረራ አናቆምም ማለት ትልቅ ቀልድ ነው። ለሚመጣው ችግር በሙሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጠያቂነቱን እንደሚወስድ ከወዲሁ ማወቅ አለበት። የሳንባ ምች (Pneomonia) እና ቲቢ እስካሁን ብዙዎችን በሚገድሉበት አገር ኮሮና ቢገባ የሚከሰተውን እልቂት ማሰብ ይዘገንናል። #StopFlyingToChina"
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 305 ደርሷል። 14,559 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ መጠቃታቸው ተሰምቷል። #nCoV @tikvahethiopia @tikvahethiopia
#UPDATE
በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 14,631 ደርሷል። ጥዋት በሰጠናችሁ መረጃ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 14,559 እንደነበር ታስታውሳላችሁ። በሰዓታት ልዩነት 72 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃጣቸው ተሰምቷል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 14,631 ደርሷል። ጥዋት በሰጠናችሁ መረጃ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 14,559 እንደነበር ታስታውሳላችሁ። በሰዓታት ልዩነት 72 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃጣቸው ተሰምቷል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ዶ/ር አብርሃም ታሪኩ ምን ይላሉ፦
የኢትዮጵያ አየር መንገድ መደበኛ በረራ በኮሮና ቫይረስ በከፍተኛ ደረጃ ወደተጠቁ ሀገራት ለጊዜው ማቆም አለበት ስንል፦
1. ኮሮና ቫይረስ አደገኛ የሳምባ ምች ሊያመጣ የሚችል እንዲሁም የመተንፈሻ አካል ስራ ማቆም ሊያስከትል መቻሉ!
2. septic shock ወይም ደም ውስጥ የሚሰራጭ ኢንፌክሽን አምጥቶ ኩላሊት ስራ እንዲያቆም አድርጎ ለሞት መዳረጉ
3. ኢንፌክሽኑ ሀገራችን ከተከሰተ ተጠጋግቶ የመኖር ባህላችን አንፃር ለመቆጣጠር በጣም ከባድ ስለሚሆን
4. የሀገራችን የንፅህና ባህል፣የተዳከመ የጤና ስርአት እንዲሁም ከምግብ አለመመጣጠን ጋር ተያይዞ ለስርጭቱ ምቹ ሊሆን ስለሚችል
5. በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ለማከም የሚያስፈልጉት የፅኑ ህሙማን መርጃ ክፍሎች (ICU rooms and beds) ፣ መተንፈሻ ማሽኖች (Mechanical ventilators) ፣ አብሮ መደረግ ያለባቸው ምርመራዎች የደም ጋዝ መጠንን (blood gas analysis) ጨምሮ በበቂ ሀገራችን ስለሌሉ በተለይ ደግሞ በሺዎች ለወረርሺኝ ከተፈለገ፤
6. የአለም የጤና ድርጅት የአለም የጤና ስጋት ብዬ ያወጅኩት ደካማ የጤና ስርአት ላላቸው ሀገራት በመስጋት ነው ማለቱ
7. የአለም የጤና ድርጅት ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ውስጥ 12 ከፍተኛ ስጋት (high risk countries) ውስጥ ማስቀመጡ
8. የመንለካው የትኩሳት መጠን ከ14 ቀናት በኋላ ሊከሰት መቻሉ
9. በበረራ ማቋረጥ ምክንያት ልናጣው ከምንችለው ገንዘብ (economy) በላይ በወረርሽኝ ብዙ ሰው ቢሞት ልናጣ የምንችለው በገንዘብ ሲሰላ ስለሚበልጥ (disease burden, disability burden and death burden)
More https://telegra.ph/DrAbrhamTariku-02-02
#HAKIM
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ መደበኛ በረራ በኮሮና ቫይረስ በከፍተኛ ደረጃ ወደተጠቁ ሀገራት ለጊዜው ማቆም አለበት ስንል፦
1. ኮሮና ቫይረስ አደገኛ የሳምባ ምች ሊያመጣ የሚችል እንዲሁም የመተንፈሻ አካል ስራ ማቆም ሊያስከትል መቻሉ!
2. septic shock ወይም ደም ውስጥ የሚሰራጭ ኢንፌክሽን አምጥቶ ኩላሊት ስራ እንዲያቆም አድርጎ ለሞት መዳረጉ
3. ኢንፌክሽኑ ሀገራችን ከተከሰተ ተጠጋግቶ የመኖር ባህላችን አንፃር ለመቆጣጠር በጣም ከባድ ስለሚሆን
4. የሀገራችን የንፅህና ባህል፣የተዳከመ የጤና ስርአት እንዲሁም ከምግብ አለመመጣጠን ጋር ተያይዞ ለስርጭቱ ምቹ ሊሆን ስለሚችል
5. በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ለማከም የሚያስፈልጉት የፅኑ ህሙማን መርጃ ክፍሎች (ICU rooms and beds) ፣ መተንፈሻ ማሽኖች (Mechanical ventilators) ፣ አብሮ መደረግ ያለባቸው ምርመራዎች የደም ጋዝ መጠንን (blood gas analysis) ጨምሮ በበቂ ሀገራችን ስለሌሉ በተለይ ደግሞ በሺዎች ለወረርሺኝ ከተፈለገ፤
6. የአለም የጤና ድርጅት የአለም የጤና ስጋት ብዬ ያወጅኩት ደካማ የጤና ስርአት ላላቸው ሀገራት በመስጋት ነው ማለቱ
7. የአለም የጤና ድርጅት ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ውስጥ 12 ከፍተኛ ስጋት (high risk countries) ውስጥ ማስቀመጡ
8. የመንለካው የትኩሳት መጠን ከ14 ቀናት በኋላ ሊከሰት መቻሉ
9. በበረራ ማቋረጥ ምክንያት ልናጣው ከምንችለው ገንዘብ (economy) በላይ በወረርሽኝ ብዙ ሰው ቢሞት ልናጣ የምንችለው በገንዘብ ሲሰላ ስለሚበልጥ (disease burden, disability burden and death burden)
More https://telegra.ph/DrAbrhamTariku-02-02
#HAKIM
@tikvahethiopia
"አየር መንገዱ ወደ ቻይና የሚያደርገውን በረራ ያቁም" - የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት
በ10 ሺህ የሚቆጠሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ [TIKVAH-ETH] ቤተሰቦች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና ከተሞች የሚያደርጋቸውን በረራዎች በአስቸኳይ እንዲያቋርጥ እየጠየቁ ይገኛሉ።
በ @tikvahethiopiaBot በኩል መልዕክት እየላኩ የሚገኙ የቤተሰባችን አባላት ለቻይና ያልተቀመሰው ይህ አደገኛ በሽታ ድሃዋ ሀገራችን ቢገባ የሚቀጥፈው የሰው ብዛት ብዙነውና አየር መንገዱ ለጊዜውም ቢሆን በረራውን ያቋርጥ ሲሉ ጠይቀዋል።
በቫይረሱ የሚሞቱ እና የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በየዕለቱ በሚጨምረበት እንዲሁም ያደጉ ሀገራት ሳይቀር ወደ ቻይና የሚያደርጉትን በረራ ባቋረጡበት በዚህ ወቅት አየር መንገዳችን ወደ ቻይና መብረር አለማቆሙ እጅግ አደገኛ ውሳኔ ነው ብለውታል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በ10 ሺህ የሚቆጠሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ [TIKVAH-ETH] ቤተሰቦች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና ከተሞች የሚያደርጋቸውን በረራዎች በአስቸኳይ እንዲያቋርጥ እየጠየቁ ይገኛሉ።
በ @tikvahethiopiaBot በኩል መልዕክት እየላኩ የሚገኙ የቤተሰባችን አባላት ለቻይና ያልተቀመሰው ይህ አደገኛ በሽታ ድሃዋ ሀገራችን ቢገባ የሚቀጥፈው የሰው ብዛት ብዙነውና አየር መንገዱ ለጊዜውም ቢሆን በረራውን ያቋርጥ ሲሉ ጠይቀዋል።
በቫይረሱ የሚሞቱ እና የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በየዕለቱ በሚጨምረበት እንዲሁም ያደጉ ሀገራት ሳይቀር ወደ ቻይና የሚያደርጉትን በረራ ባቋረጡበት በዚህ ወቅት አየር መንገዳችን ወደ ቻይና መብረር አለማቆሙ እጅግ አደገኛ ውሳኔ ነው ብለውታል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot