#ADAMA የአዳማ ከተማ የከሰዓቱን ሰላማዊ እንቅስቃሴ የቲክቫህ አዳማ ቤተሰቦች በፎቶ አስደግፈው ልከውልናል።
PHOTO: IBRO(አዳማ ቲክቫህ ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
PHOTO: IBRO(አዳማ ቲክቫህ ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA
"አዳማ ዛሬ ከነጋ ጀምሮ በሁሉም አቅጣጫ #ሠላም ነው። ሠላማዊ ህይወት እንድቀጥል ህዝባችን በማህበራዊ ሚድያ በማይታወቁ እና አከባቢው ላይ በማይገኙ ሰዎች የሚረጨውን የክፍፍል ወሬ ችላ በማለት ለሠላም ሊተጋ ይገባል።" ባይሳ(ቲክቫህ ቤተሰብ) ከአዳማ ፖስታቤት አከባቢ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"አዳማ ዛሬ ከነጋ ጀምሮ በሁሉም አቅጣጫ #ሠላም ነው። ሠላማዊ ህይወት እንድቀጥል ህዝባችን በማህበራዊ ሚድያ በማይታወቁ እና አከባቢው ላይ በማይገኙ ሰዎች የሚረጨውን የክፍፍል ወሬ ችላ በማለት ለሠላም ሊተጋ ይገባል።" ባይሳ(ቲክቫህ ቤተሰብ) ከአዳማ ፖስታቤት አከባቢ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA
የአዳማ ከተማ የዛሬ ውሎ ፍፁም የተረጋጋና ሰላማዊ ነው። የንግድ ተቋማት ወደስራቸው ተመልሰዋል፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደቀደመው ሁኔታ እየተመለሰ ይገኛል። አብዛኛው የትምህርት ተቋማት ግን ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ተማሪዎች አልተገኙም። የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደሚሉት በተማሪዎች መካከል ግጭት እንዳይፈጠር በመስጋት ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት አላኩም ብለዋል። በትላናንትናው ዕለት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከተማይቱ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷን ገልፆ በቀጣይ ቀናትም ትምህርት ቤቶች ወደ ስራ ይመለሳሉ ሲል ገልጿል።
PHOTO: IBRO(አዳማ ቲክቫህ ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዳማ ከተማ የዛሬ ውሎ ፍፁም የተረጋጋና ሰላማዊ ነው። የንግድ ተቋማት ወደስራቸው ተመልሰዋል፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደቀደመው ሁኔታ እየተመለሰ ይገኛል። አብዛኛው የትምህርት ተቋማት ግን ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ተማሪዎች አልተገኙም። የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደሚሉት በተማሪዎች መካከል ግጭት እንዳይፈጠር በመስጋት ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት አላኩም ብለዋል። በትላናንትናው ዕለት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከተማይቱ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷን ገልፆ በቀጣይ ቀናትም ትምህርት ቤቶች ወደ ስራ ይመለሳሉ ሲል ገልጿል።
PHOTO: IBRO(አዳማ ቲክቫህ ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA #JIMMA #BALE_ROBE
ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ዛሬ በአዳማ ከተማ የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። በኮንፈረንሱ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳና ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡
በተመሳሳይም በደቡብ ምዕራብ ኦሮሚያ ካሉ ዞኖችና ከተሞች የተውጣጡ ነዋሪዎች ተሳታፊ የሆኑበት የሰላም ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። በሰላም ኮንፈረንሱ ላይ ከጅማ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉ አባቦር ዞን፣ ባሌ ሮቤ እና ከጅማ ከተማ የተውጣጡ ከ1 ሺህ 600 የሚልቁ ነዋሪዎች ከክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመምከር ላይ ናቸው። በውይይቱ ላይ የኦዲፒ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እንዳሉት፥ በጥፋት ድርጊቶች ውስጥ የተሳተፉ አካላትን ለህግ በማቅረብ የህግ የበላይነት ይረጋገጣል።
ባሌ ሮቤ ላይ በተደረገው ውይይት የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትሯ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው ሰሞኑን የተፈጸመው ድርጊት ህብረተሰቡን እንደማይወክል ተናግረዋል። አያይዘውም እንደዚህ አይነት ዋጋ መክፈል እንደማያስፈልግ ጠቅሰው፥ ችግሮች ሲከሰቱ መመካከርና መደማመጥ አስፈላጊ ነው ብለዋል። ውይይቱ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የታየውን የሰላም እጦት ችግር ከመሰረቱ ይፈታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ዛሬ በአዳማ ከተማ የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። በኮንፈረንሱ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳና ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡
በተመሳሳይም በደቡብ ምዕራብ ኦሮሚያ ካሉ ዞኖችና ከተሞች የተውጣጡ ነዋሪዎች ተሳታፊ የሆኑበት የሰላም ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው። በሰላም ኮንፈረንሱ ላይ ከጅማ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉ አባቦር ዞን፣ ባሌ ሮቤ እና ከጅማ ከተማ የተውጣጡ ከ1 ሺህ 600 የሚልቁ ነዋሪዎች ከክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመምከር ላይ ናቸው። በውይይቱ ላይ የኦዲፒ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እንዳሉት፥ በጥፋት ድርጊቶች ውስጥ የተሳተፉ አካላትን ለህግ በማቅረብ የህግ የበላይነት ይረጋገጣል።
ባሌ ሮቤ ላይ በተደረገው ውይይት የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትሯ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው ሰሞኑን የተፈጸመው ድርጊት ህብረተሰቡን እንደማይወክል ተናግረዋል። አያይዘውም እንደዚህ አይነት ዋጋ መክፈል እንደማያስፈልግ ጠቅሰው፥ ችግሮች ሲከሰቱ መመካከርና መደማመጥ አስፈላጊ ነው ብለዋል። ውይይቱ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የታየውን የሰላም እጦት ችግር ከመሰረቱ ይፈታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA -- የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም ጋር በመተባበር የብሄርና የሃይማኖት ብዝሃነትን በአግባቡ ለማስተዳደር የሃይማኖት አባቶችና የህብረተሰቡ ሚና በሚል ርዕስ ያዘጋጀዉ ክልል አቀፍ ጉባኤ በአዳማ እየተካሄደ ነዉ፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA
በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የሀይማኖት መሪዎች የህዝቦችን መስተጋብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለፁ። የህዝቦች የእስር በርስ መስተጋብር እንዲጠናከርና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የተለያዩ የሀይማኖት አባቶች ተናገሩ፡፡ በዛሬው እለት ከኦሮሚያ ክልል ሁሉም አካባቢዎች የተወጣጡ የሀይማኖት ተቋማት መሪዎች እና የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካች የተገኙበት የሰላም ኮንፍረንስ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል፡፡
(ዋልታ ቴሌቪዥን)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የሀይማኖት መሪዎች የህዝቦችን መስተጋብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለፁ። የህዝቦች የእስር በርስ መስተጋብር እንዲጠናከርና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የተለያዩ የሀይማኖት አባቶች ተናገሩ፡፡ በዛሬው እለት ከኦሮሚያ ክልል ሁሉም አካባቢዎች የተወጣጡ የሀይማኖት ተቋማት መሪዎች እና የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካች የተገኙበት የሰላም ኮንፍረንስ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል፡፡
(ዋልታ ቴሌቪዥን)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ODP #ADAMA
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) የክልል አመራሮች በብልጽግና ፓርቲ ፕሮግራም እና መተዳደሪያ ህገ ደንብ ዙሪያ እየመከሩ ነው። በአዳማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ውይይት በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የኦዲፒ የዞን አመራሮች ተሳትፈዋል።
በምክክር መድረኩ በውህድ ፓርቲው ፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ህገ ደንብና የድርጅቱ አወቃቀር ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። ከዚህ ባለፈም በፓርቲው ዙሪያ በሚነሱ የተለያዩ የግልጸኝነት ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት የሚደረግ መሆኑን ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) የክልል አመራሮች በብልጽግና ፓርቲ ፕሮግራም እና መተዳደሪያ ህገ ደንብ ዙሪያ እየመከሩ ነው። በአዳማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ውይይት በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የኦዲፒ የዞን አመራሮች ተሳትፈዋል።
በምክክር መድረኩ በውህድ ፓርቲው ፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ህገ ደንብና የድርጅቱ አወቃቀር ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። ከዚህ ባለፈም በፓርቲው ዙሪያ በሚነሱ የተለያዩ የግልጸኝነት ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት የሚደረግ መሆኑን ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA
ወጣቶች "የሰላም ኃይል" በመሆን በሀገሪቷ ውስጥ የሚስተዋሉ ግጭቶች ለማስቆም የድርሻቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ። “ወጣቶች ለሰላም ”በሚል መሪ ቃል ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ ዛሬ አዳማ ከተማ ተጀምሯል።
የጉባኤው ምክትል ፀሐፊ አቶ ሂሉፍ ወልደስላሱ በኮንፍረንሱ መድረክ እንዳሉት በቅርቡ በሀገሪቱ እየተበራከቱ በመጡት ግጭቶች ውስጥ ወጣቶች ተሳታፊና ተጎጂዎችም ናቸው። በተሳሳተ መረጃና በስሜት በመገፋት ግጭቱ የሚያስከትለውን ጉዳትና ቀውስ ካለማመዘን ወጣቶች የሚሳተፉበት እንደሆነ አመላክተዋል።
“ግጭቶች በባህሪያቸው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚጎዱ በመሆኑ ችግሮቹን ለማከምና ለማስወገድ ሁላችንም አንድ ሆነን መስራት አለብን“ ብለዋል። በተለይም ወጣቶች የሰላም ኃይል መሆናቸውን ተገንዝበው በሀገሪቱ ውስጥ የሚስተዋሉ ግጭቶች ለማስቆምና አለመግባባቶች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
https://telegra.ph/ETH-12-12-2
(ENA)
@tikvahethiopia
ወጣቶች "የሰላም ኃይል" በመሆን በሀገሪቷ ውስጥ የሚስተዋሉ ግጭቶች ለማስቆም የድርሻቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ። “ወጣቶች ለሰላም ”በሚል መሪ ቃል ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፈረንስ ዛሬ አዳማ ከተማ ተጀምሯል።
የጉባኤው ምክትል ፀሐፊ አቶ ሂሉፍ ወልደስላሱ በኮንፍረንሱ መድረክ እንዳሉት በቅርቡ በሀገሪቱ እየተበራከቱ በመጡት ግጭቶች ውስጥ ወጣቶች ተሳታፊና ተጎጂዎችም ናቸው። በተሳሳተ መረጃና በስሜት በመገፋት ግጭቱ የሚያስከትለውን ጉዳትና ቀውስ ካለማመዘን ወጣቶች የሚሳተፉበት እንደሆነ አመላክተዋል።
“ግጭቶች በባህሪያቸው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚጎዱ በመሆኑ ችግሮቹን ለማከምና ለማስወገድ ሁላችንም አንድ ሆነን መስራት አለብን“ ብለዋል። በተለይም ወጣቶች የሰላም ኃይል መሆናቸውን ተገንዝበው በሀገሪቱ ውስጥ የሚስተዋሉ ግጭቶች ለማስቆምና አለመግባባቶች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
https://telegra.ph/ETH-12-12-2
(ENA)
@tikvahethiopia
#ADAMA
በአፋርና ሶማሌ ወንድማማች ህዝብ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በመፍታት እርቀሰላም ለማውረድ በሚደረገው ጥረት የአገር ሽማግሌዎችና ዑጋዞች ሚናቸውን በግንባር ቀደምነት እንዲወጡ የሰላም ሚኒስቴር አስገንዝቧል። የኢትዮጵያ የአገር ሽማግሌዎች መማክርት በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች መካከል የተፈጠረውን አለመግባበት ለመፍታት በአዳማ ከተማ ዛሬ መምከር ጀምሯል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፋርና ሶማሌ ወንድማማች ህዝብ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በመፍታት እርቀሰላም ለማውረድ በሚደረገው ጥረት የአገር ሽማግሌዎችና ዑጋዞች ሚናቸውን በግንባር ቀደምነት እንዲወጡ የሰላም ሚኒስቴር አስገንዝቧል። የኢትዮጵያ የአገር ሽማግሌዎች መማክርት በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች መካከል የተፈጠረውን አለመግባበት ለመፍታት በአዳማ ከተማ ዛሬ መምከር ጀምሯል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#KFO #OFC #ADAMA
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ [ኦፌኮ] በአዳማ ሊያደርግ የነበረው ህዝባዊ ውይይት በፀጥታ ኃይሎች መከልከሉን የአዳማ ቲክቫህ ቤተሰቦች አሳውቀውናል።
ውይይቱ ለምን? በማን? ሊከለከል እንደቻለ ግን የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ቤተሰቦቻችን ተናገረዋል። ውይይቱ ለመካፈል መጥተው የነበሩ የፓርቲው ደጋፊዎች ተቃውሞ ማሰማታቸውም ተገልጾልናል።
PHOTO : SOCIAL MEDIA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ [ኦፌኮ] በአዳማ ሊያደርግ የነበረው ህዝባዊ ውይይት በፀጥታ ኃይሎች መከልከሉን የአዳማ ቲክቫህ ቤተሰቦች አሳውቀውናል።
ውይይቱ ለምን? በማን? ሊከለከል እንደቻለ ግን የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ቤተሰቦቻችን ተናገረዋል። ውይይቱ ለመካፈል መጥተው የነበሩ የፓርቲው ደጋፊዎች ተቃውሞ ማሰማታቸውም ተገልጾልናል።
PHOTO : SOCIAL MEDIA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት መንግስት ያወጣውን መመሪያ ተላልፈው የተገኙ 443 አሽከርካሪዎችና የታክሲ ባለንብረቶች መቀጣታቸውን የአዳማ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን አስታውቋል።
መመሪያውን ተላልፈዋል በተባሉት ላይ ከተወሰደባቸው ቅጣት መካከል መንጃ ፈቃድ መንጠቅ ፣ እንዳይንቀሳቀሱ ማገድና የገንዘብ ቅጣት ይገኝበታል።
አሽከርካሪዎችና የታክሲ ባለንብረቶቹ የተቀጡት በሽታውን በሚያጋልጥ ሁኔታ ከልክ በላይ ሰዎችን በመጫን ፣ መስኮት ባለመክፈትና መጋረጃ ዘግተው ሲንቀሰቀሱ ተገኝተው ነው።
#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት መንግስት ያወጣውን መመሪያ ተላልፈው የተገኙ 443 አሽከርካሪዎችና የታክሲ ባለንብረቶች መቀጣታቸውን የአዳማ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን አስታውቋል።
መመሪያውን ተላልፈዋል በተባሉት ላይ ከተወሰደባቸው ቅጣት መካከል መንጃ ፈቃድ መንጠቅ ፣ እንዳይንቀሳቀሱ ማገድና የገንዘብ ቅጣት ይገኝበታል።
አሽከርካሪዎችና የታክሲ ባለንብረቶቹ የተቀጡት በሽታውን በሚያጋልጥ ሁኔታ ከልክ በላይ ሰዎችን በመጫን ፣ መስኮት ባለመክፈትና መጋረጃ ዘግተው ሲንቀሰቀሱ ተገኝተው ነው።
#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA
በአዳማ ከተማ ባሉ ጎዳናዎች ላይ "ከአሁን ሰዓት ጀምሮ በከተማው ውስጥ አንገብጋቢ ካልሆነ በስተቀር እንቅስቃሴ ማድረግ ተከልክሏል" የሚሉ ማስታወቂያዎች እየተነገረ መሆኑን ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግሩ።
የአዳማ ከተማ አስተዳደር ትልልቅ የድምጽ ማጉያዎችን በጫኑ መኪኖች በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች በዋና ዋና ጎዳናዎች ማስታወቂያውን እያሰራጨ መሆኑን ነው ነዋሪዎች የገለፁት።
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአዳማ ከተማ ባሉ ጎዳናዎች ላይ "ከአሁን ሰዓት ጀምሮ በከተማው ውስጥ አንገብጋቢ ካልሆነ በስተቀር እንቅስቃሴ ማድረግ ተከልክሏል" የሚሉ ማስታወቂያዎች እየተነገረ መሆኑን ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግሩ።
የአዳማ ከተማ አስተዳደር ትልልቅ የድምጽ ማጉያዎችን በጫኑ መኪኖች በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች በዋና ዋና ጎዳናዎች ማስታወቂያውን እያሰራጨ መሆኑን ነው ነዋሪዎች የገለፁት።
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አቶ ፀጋዬ ሁንዴና ወ/ሮ ኤልሳቤት አዱኛን በስልክ አግኝተናቸው ነበር በአዳማ ከተማ በሚገኘው የሳራ የንግድ ማዕከል ተከራይተው ለሚሰሩ ኢትዮጵያውን የሶስት (3) ወር ኪራይ ነፃ አድርገውላቸዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አቶ ፀጋዬ ሁንዴና ወ/ሮ ኤልሳቤት አዱኛን በስልክ አግኝተናቸው ነበር በአዳማ ከተማ በሚገኘው የሳራ የንግድ ማዕከል ተከራይተው ለሚሰሩ ኢትዮጵያውን የሶስት (3) ወር ኪራይ ነፃ አድርገውላቸዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA
በዚህ አስቸጋሪ ወቅት መተጋገዝ፣ መተባበር፣ ለወገን ደራሽ ወገን ነው በሚል አዳማ ከተማ የሚገኙት 'ቱ ብራዘርስ ፉድ ኮምፕሌክስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና አኽ-ዋን ኃ/የተ/የግ/ማህበር 5.5 ሚልዮን ብር የሚተመን የተለያዩ እገዛዎችን ማድረጋቸውን አሳውቀውናል።
- አቅም ለሌላቸው ወገኖች እንዲሆን ለአዳማ ከተማ መስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ግብረ ኃይል 500 ኩንታል መኮረኒ፣ 4000 ካርቶን ብስኩት፣ 500 ኩንታል ዱቄት አስረክበዋል።
- በድርጅቶቹ ውስጥ ለሚሰሩ ከ4,500 በላይ ሰራተኞች 10 ኪሎ ዱቄት እና 5 ኪሎ መኮረኒ ተሰጥቷል።
- በአዳማ ከተማ ለሚገኙ የህዝብ ትራንስፖርት መናኸሪያዎች ከፍተኛ ወጪ በማውጣት የእጅ መታጠቢያ በማዘጋጀት እና ህዝቡ እራሱን ከኮሮና ቫይረስ እንዲከላከል አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በዚህ አስቸጋሪ ወቅት መተጋገዝ፣ መተባበር፣ ለወገን ደራሽ ወገን ነው በሚል አዳማ ከተማ የሚገኙት 'ቱ ብራዘርስ ፉድ ኮምፕሌክስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና አኽ-ዋን ኃ/የተ/የግ/ማህበር 5.5 ሚልዮን ብር የሚተመን የተለያዩ እገዛዎችን ማድረጋቸውን አሳውቀውናል።
- አቅም ለሌላቸው ወገኖች እንዲሆን ለአዳማ ከተማ መስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ግብረ ኃይል 500 ኩንታል መኮረኒ፣ 4000 ካርቶን ብስኩት፣ 500 ኩንታል ዱቄት አስረክበዋል።
- በድርጅቶቹ ውስጥ ለሚሰሩ ከ4,500 በላይ ሰራተኞች 10 ኪሎ ዱቄት እና 5 ኪሎ መኮረኒ ተሰጥቷል።
- በአዳማ ከተማ ለሚገኙ የህዝብ ትራንስፖርት መናኸሪያዎች ከፍተኛ ወጪ በማውጣት የእጅ መታጠቢያ በማዘጋጀት እና ህዝቡ እራሱን ከኮሮና ቫይረስ እንዲከላከል አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA
በአዳማ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈጸሚያ መመሪያ ተላልፈው የተገኙ 55 አሽከርካሪዎች በገንዘብ መቀጣታቸውን በአስተዳደሩ የኮሮና መከላከል ግብረ ኃይል አሰታውቋል።
የግብረ ኃይሉ አባል ኮማንደር አለማየሁ በቀለ እንደገለጹት አሽከርካሪዎቹ የተቀጡት መመሪያውን ተላልፈው ከታሪፍ በላይ በማስከፈል፣ ትርፍ በመጫንና ከተፈደላቸው ውጭ አገልግሎት ሲሰጡ በመገኘታቸው ነው።
በዚህም 2,000 እስከ 5,000 ብር መቀጣታቸውን አመልክተዋል፡፡ ቅጣቱ ከተላለፈባቸው መካከልም የባጃጅ፣ ሚኒባስ ታክሲዎች፣ የህዝብ ማመላለሻ ዶልፊን፣ የቤት አውቶሞቢልና ከባድ የጭነት አሽከርካሪዎች ይገኙበታል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአዳማ ከተማ አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስፈጸሚያ መመሪያ ተላልፈው የተገኙ 55 አሽከርካሪዎች በገንዘብ መቀጣታቸውን በአስተዳደሩ የኮሮና መከላከል ግብረ ኃይል አሰታውቋል።
የግብረ ኃይሉ አባል ኮማንደር አለማየሁ በቀለ እንደገለጹት አሽከርካሪዎቹ የተቀጡት መመሪያውን ተላልፈው ከታሪፍ በላይ በማስከፈል፣ ትርፍ በመጫንና ከተፈደላቸው ውጭ አገልግሎት ሲሰጡ በመገኘታቸው ነው።
በዚህም 2,000 እስከ 5,000 ብር መቀጣታቸውን አመልክተዋል፡፡ ቅጣቱ ከተላለፈባቸው መካከልም የባጃጅ፣ ሚኒባስ ታክሲዎች፣ የህዝብ ማመላለሻ ዶልፊን፣ የቤት አውቶሞቢልና ከባድ የጭነት አሽከርካሪዎች ይገኙበታል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA
'የፍቅር ማዕድ' ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን!
ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን በአዳማ ከተማ ለሚገኙ 156 ወገኖች የፍቅር ማዕድ የምገባ ፕሮግራም መርሐግብርን ትላንት የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ አሰግድ እና የፋውንዴሽኑ እና የኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ሃላፊዎች በተገኙበት አስጀምረዋል።
የኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ አ.ማ. ግብረ-ሰናይ ድርጅት የሆነው ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን የአክስዮን ማህበሩ አንድ ኩባንያ ከሆነው ሬድ ፎክስ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ቢዝነስ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ለ156 የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች ለአንድ ወር የሚቆይ የምግብ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ወጪው በገንዘብ ብር 1 ሚሊዮን ይተመናል፡፡
ድጋፉ ፋውንዴሽኑ በአገሪቱ በሚገኙ ስምንት ከተሞች ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የዕለት ጉርሳቸውን ማሟላት የተቸገሩ 10,000 ወገኖችን ለመርዳት እየሰራ ያለበት የፍቅር ማዕድ የተሰኘ ፕሮጀክት አንድ አካል መሆኑን የኢስት አፍሪካን ሆልዲንግስ የፅ/ቤት ሃላፊ ና የፋውንዴሽኑ የቦርድ አባል አቶ ፍፁም ንጉሴ ገልፀዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
'የፍቅር ማዕድ' ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን!
ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን በአዳማ ከተማ ለሚገኙ 156 ወገኖች የፍቅር ማዕድ የምገባ ፕሮግራም መርሐግብርን ትላንት የአዳማ ከተማ ከንቲባ አቶ አሰግድ እና የፋውንዴሽኑ እና የኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ ሃላፊዎች በተገኙበት አስጀምረዋል።
የኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ አ.ማ. ግብረ-ሰናይ ድርጅት የሆነው ብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን የአክስዮን ማህበሩ አንድ ኩባንያ ከሆነው ሬድ ፎክስ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ቢዝነስ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ለ156 የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች ለአንድ ወር የሚቆይ የምግብ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ወጪው በገንዘብ ብር 1 ሚሊዮን ይተመናል፡፡
ድጋፉ ፋውንዴሽኑ በአገሪቱ በሚገኙ ስምንት ከተሞች ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የዕለት ጉርሳቸውን ማሟላት የተቸገሩ 10,000 ወገኖችን ለመርዳት እየሰራ ያለበት የፍቅር ማዕድ የተሰኘ ፕሮጀክት አንድ አካል መሆኑን የኢስት አፍሪካን ሆልዲንግስ የፅ/ቤት ሃላፊ ና የፋውንዴሽኑ የቦርድ አባል አቶ ፍፁም ንጉሴ ገልፀዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia