TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.5K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የፀጥታ ችግሩ መነሻ ምን እንደሆነ እንደማያውቁ የተናገሩት በአካባቢው የሚኖሩ የቤተሰባችን አባላት ተደጋጋሚ የተኩስ ድምፅ እየሰሙ እንደሆነ፣ ወጣቶች ተደራጅተውና ዱላ ይዘው ሲንቀሳቀሱ እንደተመለከቱ፣ የፀጥታ ሃይሎች ሁኔታውን ለመቆጣጠር በአካባቢው እንደተሰማሩ፣ የአምቡላንስ ድምፅ በአካባቢው እንደሚሰማ ገልፀዋል።

#video: Hils/የቲክቫህ ቤተሰብ ከቦሌ ቡልቡላ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ግብጽ እና ኢትዮጵያን እያወዛገበ ያለው በአባይ ወንዝ ላይ የሚገነባው የህዳሴ ግድብ ግንባታ ቀጥሏል። በሚቀጥለው ዓመት ኃይል ማመንጨት ይጀምራሉ የተባሉት የግድቡ ሁለት ተርባይኖች ግንባታም በመከናወን ላይ ይገኛል። የግድቡ ሰሞነኛ መልክ ምን እንደሚመስል ከቪዲዮው ይመልከቱ።

#Video: DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአንድ ሰው ግድያ ፈረንሳይን በተቃውሞ እየናጣት ነው።

በፈረንሳይ ሀገር ፓሪስ አቅራቢያ ባለፈው ማክሰኞ ዕለት አንድ የ17 ዓመት ታዳጊ በፈረንሳይ ፖሊስ መገደሉን ከተትሎ ፈረንሳያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ።

ናሄል ኤም የተሰኘው ታዳጊ በቅርብ ርቀት በፖሊስ ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን ግድያው " የትራፊክ መብራት ጥሷል " በሚል የተፈፀመ መሆኑ ተነግሯል።

ግድያውን የፈፀመው የፖሊስ አባል ፤ ሽጉጡን የመዘዘው ሕይወቱ አደጋ ላይ እንዳለ ስለተሰማው እንደሆነ ተናግሯል።

የታዳጊውን ግድያ ተከትሎ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ግን ሀገሪቱን እየናጣት ነው።

የታዳጊ መኖሪያ በሆነችው የፓሪስ አካባቢ የሚገኙ ባለሥልጣናት ሥፍራውን ለቀው ከወጡ ቀናት አልፈዋል።

በርካቶች ወደ አደባባይ ወጥተው ተቃውሞ እያሰሙ ሲሆን በዚህ መሃል ዝርፊያን ጨምሮ የአመፅ ተግባራት መፈፀማቸው ተመላክቷል።

ምንም እንኳን ታዳጊውን የገደለው የፖሊስ መኮንን ክስ ቢመሰረትም አመጹ በመላው አገሪቱ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።

- በሊል እና ማርሴ ከተሞች በርካታ ሰልፍ የወጡ ሰዎች ለእሥር በቅተዋል።

- ናንቴር በተሰኘችው ታዳጊው በሚኖርባት ከተማ አንድ ባንክ ያለበት ሕንፃ በእሳት ተቃጥሏል።

- በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ሥፍራዎች በእሣት እየጋዩ ታይተዋል።

- በፓሪስና በሌሎች ከተማዎች የአውቶቡስና ባቡር ትራንስፖርት በሃገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽት 3 ሰዓት ጀምሮ ተቋርጧል።

- አንዳንድ ከተሞች ሰዎች ምሽት እንዳንይንቀሳቀሱ የሰዓት እላፊ ገደብ ጥለዋል።

- የፈረንሳይ መንግሥት አመፁን ለመግታት 40 ሺህ የፖሊስ ሠራዊት በሃገሪቱ አሰማርቷል።

- ማክሰኞ እና ረቡዕ ምሽት በነበሩ ተቃውሞዎች በርካታ ተሽከርካሪዎችና ሕንፃዎች በእሳት ጋይተዋል።

- የሟች እናት ሐሙስ ዕለት የጠሩት ሰልፍ በርካታ ግጭቶችን አስከትሏል።

ማን ምን አለ ?

የፈረንሳይ የሃገር ውስጥ ሚኒስትሩ ዤራልድ ዳርማኒን ፥ " ረቡዕ ማታ 170 የፖሊስ መኮንኖች ጉዳት እንደደረሰባቸውና 180 ሰዎች በቁጥጥር ውለዋል። " ብለዋል።

የፈረንሳይ ጠ/ሚ ኤሊሳቤት ቦርን ፤  " በ17 ዓመቱ ታዳጊ ሞት የተነሳ የተፈጠረውን ስሜታዊነት እንረዳለን። " ያሉ ሲሆን " ግን ምንም ነገር ለአመፅ ምክንያት ሊሆን አይችልም። " ሲሉ ተናግረዋል።

የታጊው ናሄል ጠበቃ ያሲን ቦዝሩ በበኩላቸው ፤ " ሃገራችን የምትከተለው ሕግ የፖሊስ መኮንኖች የሚጠብቅ ነው። ይህ ደግሞ ያለመከሰስ ባሕልን ያዳብራል። " ሲሉ ተችተዋል።

ታዳጊውን የገደለው ፖሊስ ሽጉጡን የመዘዘው ሕይወቱ አደጋ ላይ እንዳለ ስለተሰማው እንደሆነ የተናገረ ሲሆን ጠበቃዎቹ ደንበኛቸው ድርጊቱን የፈፀመው " ሕጉን በተከተለ መንገድ ነው " ብለዋል።

#Video ከላይ የተያያዙት ቪድዮዎች የታዳጊውን ግድያ እሱን ተከትሎ በፈረንሳይ የተቀጣጠለውን ተቃውሞና አመፅ የሚያሳዩ ናቸው። (ከተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተገኙ)

Credit : BBC

@tikvahethiopia