TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" መስመሩ መበጠሱን ነው እንጂ ያረጋገጥነው በምን ምክንያት እንደተበጠሰ ማወቅ አልቻልንም " - አቶ ሞገስ መኮንን ከባህር ዳር - በደብረታቦር - ንፋስ መውጫ - ጋሸና - አላማጣ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እንዲሁም ከደብረ ብርሃን - ሸዋሮቢት - ኮምቦልቻ የተዘረጋው መስመር በመበጠሱ በሰመና መቐለን ጨምሮ በበርካታ ከተሞች ኃይል ተቋርጧል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ…
March 6, 2024
March 8, 2024
March 15, 2024
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ከ4,000 በላይ ሴቶች ተደፍረዋል ” - የአማራ ክልል ሴቶች ማኀበር የኢትዮጵያ ሴቶች ማኀበር ሴቶች ላይ እየደረሱ ናቸው የተባሉ ፈርጀ ብዙ ችግሮችን በተመለከተ በየክልሉ በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማትን በመጋበዝ ትላንት ረቡዕ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር። በዚህም ላይ ከተገኙት ባለድርሻ አካላት መካከል የአማራ ክልል ሴቶች ማኀበር አንዱ ነው። በአማራ ክልል በ “ፋኖ”…
March 17, 2024
May 13, 2024
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
May 28, 2024
June 2, 2024
June 7, 2024
#Amhara

በአማራ ክልል ዓመቱን ሙሉ ጭራሽ ምንም ያልተማሩ ተማሪዎች እንዳሉ ተሰምቷል።

በዚህም ምክንያት ምንም አይነት የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12 ክፍል ፈተና የማያስትፈትኑ ዞኖች እንዳሉ ታውቋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በሰጠው መግለጫ ፥ ከዓመቱ መጀመሪያ ጀምሮ ምንም መቆራረጥ ሳይኖር እየተማሩ አሁን ላይ ትምህርታቸውን እየጨረሱ ያሉ ተማሪዎች አሉ ብሏል።

መሃል ላይ እንዲጀምሩ የተደረጉና የይዘት ክለሳ ተደርጎ እክሰ ነሃሴ ወር ተምረው እንዲያጠናቅቁ የሚደረጉም አሉ ፤ እነሱ አሁን ትምህርት ላይ ናቸው ሲል ገልጿል።

ዓመቱን ሙሉ በሙሉ ደግሞ ጭራሽ ምንም ያልተማሩ ተማሪዎች እንዳሉ ቢሮው አሳውቋል።

ይህ በአብዛኛው በጎጃም ቀጠና እንደሆነ ተጠቁሟል።

ሰሜን ጎጃም እና ምዕራብ ጎጃም ዞኖች ምንም አይነት ተማሪ / አንድም እንኳን ተማሪ የ6ኛ ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ፈተና #እንደማያስፈትኑ ገልጿል።

ምስራቅ ጎጃም ግን ትንሽ ተማሪ አለው ተብሏል።

የትምህርት ቢሮው አሁን ላይ እየተማሩ ያሉ ግን ፈተና የማይፈተኑትን በቀጣይ በሁለተኛው ዙር እንዲፈተኑ ለማድረግ መታቀዱን አመልክቷል።

ምንም ያልተማሩ ተማሪዎችን በሚመለከት ያለ አንዳች ጥፋታቸው ከእድሜያቸው ላይ አንድ አመት መቀነሱ አገባብነት ስለሌለው የተጎዳ ስነልቦናቸውን ለመጠገን ሚያግዝ ስልጠና ይዘጋጃል ብሏል።

የይዘት ክለሳ ተደርጎም ቢሆን ሲማሩ ከነበሩ ተማሪዎች ወደኃላ እንዳይቀሩ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ሲል ገልጿል።

በአማራ ክልል የ8ኛና 6ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 4/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን ፦

184,393 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 4 እና 5 ቀን 2016 ዓ.ም

170,470 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 13 እና 14 ቀን 2016 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሏል።

በአማራ ክልል በአጠቃላይ (በሁሉም የትምህርት ደረጃ) በዚህ ዓመት መመዝገብ የነበረባቸው 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎች ውስጥ የተመዘገቡት 4 ሚሊዮን ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
June 8, 2024
June 25, 2024