TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ህጋዊ_ሰነድ እና ማስረጃ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር 116 ደረሷል፦

ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር 116 መድረሱን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አሳወቀ።

እስከ ባለፈው ሳምንት ድረስ ህጋዊ ሰነድ እና ማስረጃዎችን ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ፣ ያላመሟሉ እና ሙሉ ለሙሉ ያቀረቡ በሚል የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ማሳወቁ ይታወሳል፤ ኤጀንሲው አያይዞም የተጠየቁትን ያላቀረቡ ተቋማትን በሚመለከት እስካላቀረቡ ድረስ የያዙትን ተማሪ ከማስጨረስ በቀር አዲስ ተማሪ መመዝገብ እንደማይችሉ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።

እስከ ባለፈው ሳምንት ህጋዊ ሰነድ እና ማስረጃ ሳያመሟሉ እና ምንም ሳያቀርቡ ቀርተው የነበሩት የተቋማት ቁጥር 74 እንደነበሩ ይፋ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 18 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ የተጠየቁትን ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ማቅረባቸውን ኤጀንሲው ገልጿል። ይህም ሙሉ ለሙሉ ህጋዊ ሰነድና ማስረጃ ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር ወደ 116 ደርሷል።

የቀሩት 58 ተቋማት ህጋዊ ሰነዶቹንና ማስረጃዎቹን እስቃላቀረቡ ድረስ አዲስ ተማሪ መመዝገብ እንደማይችሉ የተላለፈው ውሳን እንተጠበቀ መሆኑን እየገለጽን ያላቀረቡትን ለይተን ዝርዝራቸውን የምናሳውቅ ይሆናል።

የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia