TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አንዲት #አሜሪካዊት በስለት #ወግቶ ገድሏል ተብሎ የተጠረጠረው ኢትዮጵያዊ ወጣት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋለ። ማርጀሪ ማጊል የተባለችው የ27 አመት አሜሪካዊት በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ባለፈው ማክሰኞ ከጀርባዋ በተደጋጋሚ ተወግታ ሕይወቷ ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል።

ፖሊስ እንዳለው ኤልያስ አረጋኸኝ የተባለ የ24 አመት ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር ውሎ የግድያ ወንጀል ፈፅሟል የሚል ክስ ተመስርቶበታል። የዋሽንግተን ዲሲ ፖሊስ አዛዥ ፒተር ኒውስሐም መርማሪዎች ወንጀሉ በተፈጸመበት አካባቢ የሚገኙ የጸጥታ ካሜራዎች የቀረጿቸውን ምስሎች ከተመለከቱ በኋላ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር እንዳዋሉ ተናግረዋል። ተጠርጣሪው ለምን ወንጀሉን እንደፈጸመ እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።

Via #ShegerTribune
@tsegabwolde @tikvahethiopia