TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የድሬዳዋ ሪፈራል ሆስፒታል!

በ2002 ዓ.ም ግንባታው ተጀምሮ #ዛሬም ድረስ ያልተጠናቀቀው የድሬዳዋ ሪፈራል ሆስፒታል ለድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ተሰጠ። ሆስፒታሉ ዛሬ በተካሄደ ስነ ስርዓት ወደ ዩኒቨርስቲው እንዲተላለፍ የተደረገው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በወሰነው መሰረት ነው።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የሆስፒታሉን ቀሪ የግንባታ ስራዎችን አጠናቅቆ የህክምና ማስተማርያና እና ምርምር ማዕከል እንደሚያደርገው በዛሬው የርክክብ ስነ ስርዓት ተገልጿል። የርክክብ ሰነዱን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አህመድ መሀመድ ቡህ እና የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ያሬድ ማሞ ተፈራርመዋል። ዶ/ር ያሬድ ዩኒቨርስቲው የሆስፒታሉን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ 200 ሚሊዮን ብር በጀት መመደቡን ተናግረዋል። በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የግንባታ ስራውን እንደሚያጠናቅቅም ገልጸዋል።

በ324 ሚልዮን ብር በጀት ግንባታው ሲከናወን መቆየቱ የተገለጸው የድሬዳዋ ሪፈራል ሆስፒታል ሲጠናቀቅ ከሶስት መቶ በላይ አልጋዎች እና የተለያዩ የህክምና ማዕከላት ይኖሩታል። ሆስፒታሉ ወደ ዩኒቨርስቲው እንዲዛወር መደረጉ ለከተማይቱ እና አጎራባች አካባቢ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችል ተቋም ያደርገዋል ተብሏል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓታት የትኞቹ የዓለማችን ሀገራት ከፍተኛ የኮቪድ-19 ሞት አስተናገዱ ?
ምን ያህል ዜጎቻቸው በቫይረሱ ተያዙ ?

1ኛ. አሜሪካ : 3,912 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 151,727 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

2ኛ. ሜክሲኮ : 1,743 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 17,165 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

3ኛ. ዩናይትድ ኪንግደም : 1,725 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 25,308 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

4ኛ. ብራዚል : 1,319 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 63,895 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

5ኛ. ጀርመን : 986 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 15,611 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

6ኛ. ደቡብ አፍሪካ : 753 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 7,070 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

7ኛ. ሩሲያ : 594 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 17,741 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

8ኛ. ስፔን : 492 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 40,285 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

9ኛ. ጣልያን : 467 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 15,204 ዜጎቿ በይረሱ ተይዘዋል።

10ኛ. ኮሎምቢያ : 395 ዜጎቿ ሞተዋል ፤ 13,953 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

በአጠቃላይ በዓለማችን ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 16,852 ሰዎች ሲሞቱ 590,732 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሪፖርት ተደርጓል። በሌላ በኩል የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከተቀሰቀሰ ጊዜ አስንቶ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 101,441,979 የደረሱ ሲሆን ከነዚህ መካከል ከ2.1 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሞተዋል፤ ከ73.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አገግመዋል።

#ዛሬም_ጥንቃቄ_አይለያችሁ!

#Purpose #Tikvah

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT