TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም አገግመው ወደ ቤታቸው ተመለሱ ተባለ!

#በአስመራ በተደረገባቸው የግድያ ሙከራ ቆስለዋል ተብለው የነበሩት የኤርትራ የማዕድን ምኒስትር ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም አገግመው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን በጃፓን የኤርራ አምባሳደር #እስጢፋኖስ_አፈወርቂ አስታወቁ። ጄኔራል ስብሃት በአስመራ ከተማ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸዋል የተባለው ባለፈው ታኅሳስ 2011 ዓ.ም. ነበር። በኤርትራ ላይ የሚያተኩሩ እና በተቃዋሚዎች የሚተዳደሩ ማኅበራዊ ድረ-ገፆች ጄኔራሉ በሽጉጥ ጭንቅላታቸው ላይ ተመተው መቁሰላቸውን ፅፈው ነበር።

የኤርትራ መንግሥት በአገሪቱ የትጥቅ ትግል ከፍ ያለ ሚና እንደነበራቸው በሚነገርላቸው ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም ላይ ተሞከረ ስለተባለው ግድያ በይፋ የሰጠው ማብራሪያ አልነበረም። አምባሳደር እስጢፋኖስ አፈወርቂ «ጄኔራል ስብሃት ኤፍሬም በውጭ ሀገር ከተደረገላቸው ስኬታማ ሕክምና በኋላ አገግመው ከውድ ቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ አስመራ መመለሳቸውን በመስማቴ ደስ ብሎኛል» ሲሉ በትዊተር ገፃቸው አስፍረዋል። አምባሳደሩ የማዕድን ምኒስትሩ ሕክምና የተደረገላቸው የት እንደሆነ በይፋ ያሉት ነገር የለም። በአስመራ ከተማ በጄኔራል ስብሃት ላይ ጥቃቱ መፈጸሙ ከተሰማ በኋላ የተሰራጩ መረጃዎች ለሕክምና ያመሩት ወደ ዱባይ እንደነበር ይጠቁማሉ።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia