TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የጎዳና ተዳዳሪዎች በዝቅተኛ ደሞዝ ሥራ አንይዝም አሉ!

የአዲስ አበባ ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ በመልሶ ማቋቋም ካሰለጠናቸው የጎዳና ተዳዳሪዎች ውስጥ ከ500 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ወደ ሥራ ለመግባት የቀረበልን ደመወዝ ዝቅተኛ ነው በማለት ያለሥራ በካምፕ ውስጥ መቀመጣቸውን አስታወቀ።

ተማሪዎቹ ሰልጥነው ወደ ሥራ ሲገቡ በዝቅተኛው ደሞዝ ማለትም በ1 ሺሕ 700 ብር የሚቀጠሩ ከሆነ በኮካ ኮላ የመጠጥ ፋብሪካ የሚከፈል ሰባት መቶ ብር የቤት ኪራይ ለሰባት ወር ቢዘጋጅም ፈቃደኛ ያለመሆናቸው ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ የማኅበራዊ ደኅንነት ልማት ማስፋፍያ ዳይሬይክተር እንደሻው አበራ ለአዲስ ማለዳ እንዳስታወቁት በመልሶ ማቋቋም ከሰለጠኑ 966 ተማሪዎች ውስጥ 225ቱ በሥራ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ሠልጥነው የተለያዩ ሥራዎች ከተቀጠሩት ሠልጣኞች ውስጥም ከ1 ሺሕ 700 ብር እስከ 11 ሺሕ ብር ደሞዝ በተለያዩ ድርጅቶች ያስቀጠረ ሲሆን ሥራ ካላገኙ ተማሪዎች በተጨማሪ በዝቅተኛ ደሞዝ ሥራ መጀመር አንችልም ብለው ያለ ሥራ የተቀመጡ ተማሪዎችም እንዳሉ አስታውቀዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇#ማለዳአዲስ
https://telegra.ph/E-08-12-2