TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Breaking የኦሳማ ቢላደን ልጅ የሆነው ሀምዛ ቢላደን መሞቱን የአሜሪካ ባለስልጣናት ተናገሩ። ስለአሟሟቱ የት? በምን ሁኔታ? እንደሞተ ይፋ የተደረገ መረጃ የለም።

https://www.nytimes.com/2019/07/31/us/politics/hamza-bin-laden-al-qaeda.html?smid=fb-nytimes&smtyp=cur&fbclid=IwAR1S_u6NVYSc8AL8X6MDer6RsSt56VbDcnh1faSW5DKEGEA78LB6DuReHNA

Via The New York Times
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ውድ የብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎችና ቤተሰቦች የኤጀንሲያችንን ማህበራዊ ገጾች በማስመሰል የተለያዩ የተዛቡ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎችንና የተማሪ ወላጆችን ሲያምታቱ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በአሁኑ ወቅትም የከፍተኛ ትምህርት መግብያ የፈተና(12ኛ ክፍል ፈተና) ውጤት ተለቋል በማለት እያደናገሩ ይገኛሉ፡፡ ይህ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን እየገለጽን የፈተና ውጤቱ በሚለቀቅበት ወቅት እንደተለመደው በኤጀንሲው የማህበራዊ ገጽና ከዚህ ቀደም ውጤት የምንገልጽበት ዌብ ሳይት www.neaea.gov.et የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡"

የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣሉ::

ምንጭ፦ ጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#SMN የሲዳማ ሚዲያ ኔትወርክ አመራሮች ታሪኩ ለማና ጌታሁን ደጉዬን ጨምሮ 9 ተጠርጣሪዎች ዛሬ በሐዋሳ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ። በሲዳማ ዞን 935 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ዳኛቸው ደምሴ ተናግረዋል።

Via #እሸት_በቀለ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ያገባኛል ይመለከተኛል

ልጆቻንን ከጎዳና ህይወት ለማውጣት በኢትዮጵያውያን ወንጌላውያን መሪዎች ህብረት የተዘጋጀ የመዝሙር ኮንሰርት
ነሐሴ 4 /2011
ከ8:00 እስከ ምሽት 1:00
የመግቢያ ዋጋ መደበኛ 100 ብር
VIP 1000 ብር
ገቢው የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ማህበራዊ ትረስት ፈንድን ለመደገፍ ይውላል
#ያገባኛል_ይመለከተኛል

"ያገባኛል-ይመለከተኛል" በሚል መሪ ቃል እስከ 100 ሚሊዮን ብር ገቢ የሚያስገኝ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው፡፡ ዝግጅቱን የአዲስ አበባ ከተማ ማህበራዊ ትረስት ፈንድ እና የኢትዮጵያ ኢቫንጂሊካል ሊደርስ ፊሎ ሺፕ በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን በሚሊንየም አዳራሽ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የቀድሞ የሱዳን ፕሬዝዳንት ኦማር አል-በሽር የሙስና ክስ ችሎት እ.አ.አ ነሐሴ 17/2019 እንደሚጀመር ጠበቃቸው ሒሻም አል-ጋሊ ገልጸዋል። ችሎቱ ለነሐሴ 17 የተላለፈው ፕሬዝዳንቱ በመጀመሪያው ችሎት ላይ ትናንት ፍርድ ቤት ባለመቅረባቸው ነው። አል-በሽር ፍርድ ቤት መቅረብ ያልቻሉት በደህንነት ስጋት ምክንያት መሆኑን ጠበቃው ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ሲጂቲኤን አፍሪካ/#etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ሳተላይት ልታመጥቅ ነው!

ኢትዮጵያ ከጥቂት ወራት በኋላ የመሬት ምልከታ ሳተላይት ልታመጥቅ መሆኗን አስታውቃለች። በመሬት ያሉ ነገሮችን እና ስለመሬት መረጃ የምታሰባስብ በኢትዮጵያውያን እና በውጭ ሀገራት ምሁራን የተሰራች ሳተላይት ለማምጠቅ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-01

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ሜዳ ቻት እና አበበች ጎበና በመተባበር በሜዳ መዋጮ ለአበበች ጎበና የህፃናት ማሳደጊያና መንከባከቢያ ማዕከል ብር የማዋጫ መንገድ ሜዳ ቻት ላይ አዘጋጅተዋል

ሜዳ ቻትን በስልኮ ላይ ጭነው @abebechgobena ብለው ይፈልጉና የቻናሉ ዝርዝር ውስጥ በመግባት የቻሉትን ያህል ለማዕከሉ ይደግፉ
ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ማን ናቸው? 

https://telegra.ph/ክብርት-ዶር-አበበች-ጎበና-ማን-ናቸው-07-31
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር!

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት #ሳህለወርቅ_ዘውዴ በአሁን ሰዓት የቀይ መስቀልን የስራ እንቅስቃሴ በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ።

Via Mandefro Negash/TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሀረር

የምሥራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች ክልሎች የጸጥታ ምክር ቤት የምክክርና የሰላም መድረክ በሐረር ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ የአጎራባች ክልልች ተወካዮችና የጸጥታ አካላት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቤኒሻንጉል_ጉምዝ

ለኢንቨስትመንት መሬት ከወሰዱና ከአላለሙ ባለሃብቶች በመንጠቅ ለአልሚ ባለሀብቶችና ለወጣቶች እንደሚሰጥ የቤኒሻንጉል ክልል ምክር ቤት አስታወቀ፡፡

ምክር ቤቱ ከትናንት በስቲያ ማክሰኞ በጀመረው የ5ኛ 5 ዓመት 5ኛ የስራ ዘመን 9ኛ ጉባኤም የአስፈጻሚ አካላት ሪፖርት ሲገመግም እንደገለጸው፣ በተለይ የግብርናውንና የማዕድን ዘርፍ ስራዎችን ለመስራት መሬት ወስደው ያላለሙት ይነጠቃሉ፤ ለወጣቶችና ለአልሚ ባለሃብቶችም ይሰጣል፡፡

የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ታደሰ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ ክልሉ የበርካታ ጸጋዎች ባለቤት እንደሆነ ጠቅሰው፤ በተለያዩ ዘርፎች ማልማት የሚፈልጉ ባለሃብቶች መሬት ተረክበው መሰማራታቸውን ተናግረዋል፡፡

Via አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
/በአለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት/

#ScamPageAlert

ፌስቡክ ላይ "Adey Foreign Employment Agency" በሚል ስም ትልልቅ የውጭ ኩባንያዎችን እየጠቀሰ ስራ እናስቀጥራለን፣ ቪዛ እናስገኛኛኘን እንዲሁም የመኖርያ ፈቃድ እናሰጣለን የሚል ገፅ አለ። ገፁ በሀሰት መረጃ ሰዎችን እያጭበረበረ እንደሆነ እንዲሁም የሚጠቅሳቸው የውጭ ኩባንያዎች እንዲህ የሚባል ድርጅት እንደማያውቁ ተደርሶበታል።

ጠንቀቅ እንበል!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከADEY የተሰጠ ምላሽ፦

🏷እኛ #Adey_Foreign_Employment_Agency የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚያውቀውን #ህጋዊ ኤጀንሲ ነን፤ ማንኛውም ህጋዊነታችንን ማረጋገጥ የሚፈልግ ሰው የምንሰራበት ቦታ ድረስ መጥቶ ማረጋገጥ ይችላል፤ የተባለው ነገር ስህተት ነው ሊታረም ይገባል ሲሉ ለTIKVAH-ETH ተናግረዋል።

ይህንንም መረጃ አያይዘው ልከዋል፦

PHON:-+251-11-551-70-80 or +251-11-551-83-79
email:[email protected]
website:- www.mols.gov.et
Facebook:-Ministry of Labor and Social Affairs
Located in kirkos sub-city Wereda 8, Kazanchis

🏷ከአለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት በኩል የሚሰጥ ምላሽ ካለ ተከታትለን እናቀርባለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በ2011 የበጀት አመት አጠናቅቃቸዋለሁ ያላቸውን 11 ፕሮጀክቶች በጨረታ ሒደት መጓተትና በወሰን ማስከበር ችግሮች የተነሳ መጨረስ አለመቻሉን ተናገረ፡፡ በበጀት አመቱ 4 ቢሊዮን ብር ለወሰን ማስከበር ስራ ወጪ ማድረጉንም ተናግሯል፡፡

Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
“ከተማዋ ሌሊት መተኛት የለባትም”-ዶ/ር #ሰለሞን_ኪዳኔ

#አዲስ_አበባ

በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የተደረገው የትራንስፖርት ስርዓቱን ለማሳለጥ የወጣው መመሪያ ሌሊት ጭምር የስራ እድል እንዲፈጠር የሚያስችል በመሆኑ ‹‹ከተማዋ ሌሊት መተኛት የለባትም፡፡” ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪና የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ገለጹ፡፡

ኃላፊው ዶክተር ሰለሞን ኪዳኔ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ በአዲስ አበባ ከተማ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ሊኖር የሚገባው ቀን ብቻ አይደለም፡፡ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ 24 ሰዓት ሊኖር ይገባል፤ አንዱ ሲተኛ ሌለው ወደ ስራ የሚገባበት ከተማ ልትሆን ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።

‹‹አሁን ባለው ሁኔታ ከተማዋ ሌሊት የምትተኛ ነች›› ያሉት ዶክተር ሰለሞን ነገር ግን ከተማዋ ልትተኛ አይገባም፤ የተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴ በሰዓት የሚገድበው መመሪያም ከተማዋ እንዳትተኛና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲኖር እንደሚያስችል አንስተዋል፡፡

Via አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakePage የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ከህጋዊው የፌስቡክ ገፅ ውጪ የቴሌግራም ገፅ የለውም። የተለያዩ አካላት ሀሰተኛ ገፆችን በመክፈት ተማሪዎችንና የተማሪ ወላጆችን ሀሰተኛ መረጃ በማቀበል እያወዛገቡ ይገኛሉ። ስለሆነም ጥንቃቄ እድታደርጉ እንላለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሲዳማ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጆችን ጨምሮ በሐዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች በተቀሰቀሱ ግጭቶች እጃቸው አለበት የተባሉ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ተጠርጣሪዎቹ በእስር እና በምርመራ ወቅት «ዛቻና ማስፈራሪዎችን ጨምሮ የተለያዩ የመብት ጥሰቶች እየተፈጸሙብን ይገኛል» ሲሉም ለፍርድ ቤት አቤት ብለዋል።
.
.
የመርማሪ ፖሊስ ግለሰቦቹን በሀዋሳ ከተማና በሲዳማ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ከሀምሌ 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት በተከሰቱ ሁከቶች ለጠፋው የሰው ህይወትና ንብረት ጠርጥሪያቸዋለሁ ሲል ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል።
.
.
ተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ ለመመስረትም የምስል ፣ የድምፅ እና የሰነድ ማሰረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ እንደሚገኝ ለችሎቱ ያስረዳው መርማሪ ፖሊስ «ቀሪ የምርመራ ሰራዎችን ለማካሄድ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠኝ» ሲልም ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Hawassa-08-01
የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የፈተና ውጤት ገና ይፋ አልተደረገም!

የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የፈተና ውጤት ገና ይፋ አለማድረጉን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በአሁኑ ወቅት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ወይም የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ተለቋል በማለት እየተሰራጨ ያለው ወሬ የተሳሳተ መረጃ መሆኑን የኤጀንሲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ረዲ ሺፋ ለኢቲቪ ገልፀዋል።

የ12ኛም ሆነ የ10ኛ ክፍል የፈተና ውጤት በሚለቀቅበት ወቅት ኤጀንሲው በፌስ ቡክ ገፁ እና በድረገፁ www.neaea.gov.et ይፋ የሚያደርግ መሆኑን አቶ ረዲ አመልክተዋል። የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ቀድመው ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስለሚገቡና የተፈታኞቹ ቁጥር ከአስረኛ ክፍል ተፈታኞች ቁጥር አንፃር አነስተኛ በመሆኑ ውጤታቸውን ቀድሞ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በመሆኑም የብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች የኤጀንሲውን ማህበራዊ ገጾች በማስመሰል ከሚለቀቁ የተለያዩ የተዛቡ መረጃዎች እንዳይወናበዱ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

Via #etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert በቢሯቸው በተፈጸመ #ጥቃት ቆስለው በወታደራዊ አውሮፕላን ለሕክምና ወደ ኳታር የተወሰዱት የሞቃዲሾ ከንቲባ አብዲራሕማን ኦማር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
.
.
የሞቃዲሾ ከንቲባ አብዲራሕማን ኦማር በቢሯቸው በተፈጸመ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት መቁሰላቸው ይታወሴ። በወቅቱ ጥቃቱ ሲፈጸም በከንቲባው ቢሮ በጸጥታ ጉዳይ ላይ ውይይት እየተደረገ አይዘነጋም።

Via #Eshete_Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia