TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የስራ ማቆም አድማ መቱ...

#የኮይሻ_ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ሠራተኞች የስራ ማቆም አዱማ ከአምስት ሺህ በላይ የኮይሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ሠራተኞች የስራ ማቆም አዱማ ከመቱ ሁለተኛ ሳምንት መያዙን ተናገሩ፡፡
 
ሰራተኞቹ ሥራ አቆምን ያሉት በሚደረስባቸው የአስተዳደር በደል ፣ ከደመወዝና ጥቅማጥቅም ጋር በተያያዙ ችግሮች ሲሆን በደል አድርሰውብናል ያሏቸው ስድስት የፕሮጀክቱ ኃላፊዎች እንዲባረሩ ይጠይቃሉ፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ጥያቄቸው ተገቢ ባይሆንም ከምግባቸው ላይ የሚቀነሰውን ገቢ ግብር ሳሊኒ ኩባኒያ እንዲሸፍን፤ በደመወዛቸው ላይ ደግሞ 450 ብር እንዲጨመር ተማምነናል ብሏል፡፡

የፕሮጀክቱ ሥራ መቀጠል ስላለበት ይህንን የማይቀበሉ ሠራተኞች እንደሚሰናበቱ ተወስኗልም ተብሏል፡፡

በህግና በማስረጃ እንጂ የደቦ ፍትህ በመፈለግ ስድስት የፕሮጀክቱ ኃላፊዎች ይባረሩ ማለታቸው ስህተት ነው ብሏል፡፡

Via #VOA24
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሥራ ማቆም አድማ መትተዉ የነበሩት #የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ሠራተኞች ወደ ሥራ ገበታቸዉ ለመመለስ #ተስማሙ። የአሠሪዉ ኩባንያ ኃላፊዎችና የሠራተኞቹ ተወካዮች በተከታታይ ሲደራደሩ ነበር። የሠራተኞቹ ተወካዮች ለDW እንደነገሩት ሠራተኞቹ ነገ #ሥራ ለመጀመር ተስማምተዋል። ሠራተኞቹ አድማዉን አቁመዉ ወደ ሥራ ለመመለስ የወሰኑት በደል አድርሰዉብናል በማለት ቅሬታ አቅርበዉባቸዉ ከነበሩ ኃላፊዎች ሁለቱን አሠሪዉ ድርጅት ከሥራ #በማገዱ ነዉ። የዶቸ ቬለ ምንጮች እንዳረጋገጡት እገዳ የተጣለባቸው ሁለቱ ኃላፊዎች ግድቡን በኮንትራት በሚገነባዉ በሳሊኒ ኩባንያ ወስጥ በከፍተኛ የሰው ሀብትና የፋይናንስ ኃላፊነት ቦታዎች ላይ ይሠሩ የነበሩ ናቸዉ።ወደ ስድስት ሺሕ የሚጠጉ የኮይሻ ግድብ ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ የመቱት ባለፈዉ ሳምንት ማብቂያ ነበር።

@tsegabwolde @tikvahethiopia