TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ETHIOPIA

የግብረ ሰዶም ጥቃት ያደረሰዉ ታዳጊ በ13 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ!
.
.
ተከሳሽ የ16 ዓመቴ ታዳጊ ወጣት #ናሆም_መሀሪ የተመሳሳይ ጸታ ግንኙነት ወንጀል በመፈጸሙ በዓቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል፡፡ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 631/1/ለ/ ሥር የተደነገገዉን በመተላለፍ ተከሳሽ ከእርሱ ጋር ተመሳሳይ ጾታ ካለዉ ወንድ ልጅ ጋር የግብረሰዶም ጥቃት ለመፈጸም በማሰብ ጥር 16 ቀን 2011ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ሲሆን በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ቦታዉ ካራ ስጋ መሸጫ አካባቢ በ8ዓመቱ ህፃን ላይ የፈጸመዉን የግብረሰዶም ጥቃት በማስረጃ በማረጋገጡ ነዉ ዓቃቤ ህግ ክሱን የመሰረተዉ፡፡

ተከሳሽ ህጻኑን አባብሎና አታሎ ድርጊቱን ፈጽሞል በግል ተበዳይ ላይም የአካል እና የስነልቦና ጉዳት እንዲደርስበት ምክንያት ሆኗል ሲል ዓቃቤ ህግ በክሱ አስረድቷል፡፡የግል ተበዳይም በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የህክምና ምርመራ ተደርጎለት ወሲባዊ ጥቃት እንደተፈጸመበት ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ጉዳዩን ሲከታተል የቆየዉ የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የካ ምድብ ችሎትም የወንጀሉን መፈጸም በሰዉና ከጋንዲ ሆስፒታል በተገኘ የህክምና ማስረጃ አረጋግጦ የጥፋተኝነት ብይን ሰጥቷል፡፡

በዚህም መሰረት ተከሳሹ #ጥፋተኛ የተባለበት የህግ ድንጋጌ ደረጃና እርከን ስላልወጣለት መነሻዉ ከ16 ዓመት ጀምሮ የሚያስቀጣ ቢሆንም የጥፋተኛዉን እድሜ ከግምት በማስገባት ሰኔ 25 ቀን 2011ዓ.ም በዋለዉ 5ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሹ በ13 ኣመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

Via የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia