#update በዜግነትና በማህበራዊ ፍትህ ዙሪያ እሰራለሁ ብሎ በቅርቡ የተቋቋመው “#ኢዜማ” ዛሬ በጉባኤ የተመረጡ አባላቱን ይፋ ያደርጋል ተባለ፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበር የሸዋስ አሰፋ ለሸገር ራድዮ እንደተናገሩት የፓርቲው ከፍተኛ መሪዎች ከአባላት ጋር ዛሬ የሚተዋወቁበትን ፕሮግራም አዘጋጅተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ በቅርቡ የተመሰረተ ሲሆን የፓርቲውን ሊቀመንበርና መሪ መምረጡ ይታወቃል፡፡ በፓርቲው መሪና በፓርቲው ሊቀመንበር መሀከል ግልፅ ልዩነቶችን በማስቀመጥ የመንግስትና የፓርቲ ስራ እንዲለይ ተደርጎ የተመሰረተ ፓርቲ ነውም ተብሏል፡፡
Via #ሸገርራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #ሸገርራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢዜማ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ/#ኢዜማ/ በሀገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በነገው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳውቋል። መግለጫውን የሚሰጠው ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ በቅሎ ቤት አካባቢ በሚገኘው የኢዜማ ጽሕፈት ቤት እንደሆነ ነው ፓርቲው የገለፀው። በሚሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሁሉም የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙሃን እንዲገኙም ጥሪ አስተላልፏል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ/#ኢዜማ/ በሀገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በነገው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳውቋል። መግለጫውን የሚሰጠው ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ በቅሎ ቤት አካባቢ በሚገኘው የኢዜማ ጽሕፈት ቤት እንደሆነ ነው ፓርቲው የገለፀው። በሚሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሁሉም የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙሃን እንዲገኙም ጥሪ አስተላልፏል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢዜማ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህብራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በ16 መስኮች የመጀመሪያ ደረጃ ረቂቅ ፖሊሰዎችን ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል።
የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ፥ ፖሊሲዎቹ ከ70 በላይ በሚሆኑ ምሁራን መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ምሁራኑ መንግስት እየተመራባቸው ያሉ ፖሊሲዎችን በዝርዝር እና በጥልቀት በመገምገም፤ የመጀመሪያ ደረጃ ሪቅቅ ፖሊሲ አዘጋጅተው አቅርበዋል።
በግብርና፣ ኢንደስትሪ፣ቱሪዝም፣ ትምህርት፣ የውጭ ጉዳይ፣ ንግድ እና ሌሎች መሰኮች ላይ በተዘጋጀው ሪቂቅ ፖሊሲ ላይም የፓርቲው አመራሮች ከምሁራኑ ጋር ውይይት አካሂደዋል።
ረቂቅ ፖሊሲው በፓርቲው አመራሮች እና በአዘጋጅ ምሁራን በዝርዝር ከተመከረበት በኋላ፤ በፓርቲው የተለያዩ መዋቅሮች ደረጃ ውይይት እንደሚካሄድበትም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
ከፓርቲው አባላት ጋር ከሚደረግ ውይይ በኋላ ረቂቅ ፖሊስው ስልጣን ባለው የፓርቲው አካል ፀደቆ የኢዜማ የፖሊሲ ሰነድ እንደሚሆንም ተነግሯል።
የኢዜማ መሪ ፕሮፌስር ብርሃኑ የፖለሲ ዝግጅቱ የፓርቲው የምርጫ ዝግጅት አካል ይሆን ወይ ተብለው ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፥ ምርጫው በየትኛውም ጊዜ ይካሄድ ፓርቲው ፖሊሲዎችን የማዘገጃት ግዴታውን እየተወጣ ነው ብለዋል።
ሰለቀጠዩ ምርጫም በሰነዘሩት ሃሳብም የምርጫው ማከናወኛ ወቅት ከጊዜ ይልቅ በሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ቢወሰን የተሻለ ነው ብለዋል።
በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላም እና መረጋጋት መስፈኑ፣ ፓርቲዎች በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በነፃነት ለመንቀሳቀስ የሚችሉበት አውድ መኖር እና ምርጫ ቦርድ ትክክልኛ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ማረጋገጫ መስጠቱ፤ የምርጫውን መከወኛ ጊዜን የመወሰን አቅም እንዳለቻውም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህብራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በ16 መስኮች የመጀመሪያ ደረጃ ረቂቅ ፖሊሰዎችን ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል።
የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ፥ ፖሊሲዎቹ ከ70 በላይ በሚሆኑ ምሁራን መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ምሁራኑ መንግስት እየተመራባቸው ያሉ ፖሊሲዎችን በዝርዝር እና በጥልቀት በመገምገም፤ የመጀመሪያ ደረጃ ሪቅቅ ፖሊሲ አዘጋጅተው አቅርበዋል።
በግብርና፣ ኢንደስትሪ፣ቱሪዝም፣ ትምህርት፣ የውጭ ጉዳይ፣ ንግድ እና ሌሎች መሰኮች ላይ በተዘጋጀው ሪቂቅ ፖሊሲ ላይም የፓርቲው አመራሮች ከምሁራኑ ጋር ውይይት አካሂደዋል።
ረቂቅ ፖሊሲው በፓርቲው አመራሮች እና በአዘጋጅ ምሁራን በዝርዝር ከተመከረበት በኋላ፤ በፓርቲው የተለያዩ መዋቅሮች ደረጃ ውይይት እንደሚካሄድበትም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
ከፓርቲው አባላት ጋር ከሚደረግ ውይይ በኋላ ረቂቅ ፖሊስው ስልጣን ባለው የፓርቲው አካል ፀደቆ የኢዜማ የፖሊሲ ሰነድ እንደሚሆንም ተነግሯል።
የኢዜማ መሪ ፕሮፌስር ብርሃኑ የፖለሲ ዝግጅቱ የፓርቲው የምርጫ ዝግጅት አካል ይሆን ወይ ተብለው ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፥ ምርጫው በየትኛውም ጊዜ ይካሄድ ፓርቲው ፖሊሲዎችን የማዘገጃት ግዴታውን እየተወጣ ነው ብለዋል።
ሰለቀጠዩ ምርጫም በሰነዘሩት ሃሳብም የምርጫው ማከናወኛ ወቅት ከጊዜ ይልቅ በሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ቢወሰን የተሻለ ነው ብለዋል።
በሀገሪቱ አስተማማኝ ሰላም እና መረጋጋት መስፈኑ፣ ፓርቲዎች በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በነፃነት ለመንቀሳቀስ የሚችሉበት አውድ መኖር እና ምርጫ ቦርድ ትክክልኛ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ማረጋገጫ መስጠቱ፤ የምርጫውን መከወኛ ጊዜን የመወሰን አቅም እንዳለቻውም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቐለ⬆️
ዛሬ መስከረም 4/2012 ዓ.ም፣ #ኢዜማ በመቐለ ከተማ ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል።
Via ኢዜማ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ መስከረም 4/2012 ዓ.ም፣ #ኢዜማ በመቐለ ከተማ ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል።
Via ኢዜማ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#SomaliPP
በሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ምን ተፈጠረ ? ፓርቲው ለሁለት ተከፍሏል ?
የሶማሌ ክልል የኮሚኒኬሽን ምክትል ኃላፊ አቶ መሀመድ ሮብሌ ፦
" ... ከዚህ በፊት በተለያዩ ቦታ ተሰጥቷቸው በክልሉ በቢሮ ኃላፊ እና በምክትል ኃላፊነት ደረጃ የነበሩና ከዛ በኃላ በነበሩ ግድፈቶች እና ድክመቶች ስራቸውን በትክክል አለመስራት ፣ በሙስና፣ በተለያዩ ምክንያቶች ከስልጣን የተባረሩ ሰዎች ናቸው።
ተሰባስበው Issue ለመፍጠር ሲሉ ነው እንጂ በፓርቲው መሃል ምንም የተፈጠረ ችግር የለም።
እነዚህ Alredy ከሲስተም የወጡ ሰዎች ናቸው። ምናልባት አንዳንድ በትክክለኛ መንገድ ተገምግመው ያልተባረሩ ሰዎች እዛ ውስጥ ሊኖሩ ይችላሉ ፤ ሌላው ግን በትክክል ከሲስተም የወጡና ህብረተሰቡን ማገልገል ሳይችሉ ፣ የተሰጣቸውን ስራ መስራት ሳይችሉ ቀይርተው የተባረሩ ናቸው። "
የሶማሌ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የፅ/ቤት ኃላፊ እንጂነር መሀመድ ሻሌ ፦
" ... እኛም በሶሻል ሚዲያ ያየነው ነገር አለ። የነበረ ነገር ግን ከለውጡ ወዲህ የተለያዩ እርምጃዎች ሲወሰዱ ነበር ከስነምግባር እና ከሙስና ጋር በተያያዘ በዚህም ከስልጣን የተነሱ ሰዎች አሉ።
ትላንትና መግለጫ አውጥተዋል ተብለው በሶሻል ሚዲያ ያየኃቸው ሰዎች ነበሩ። አብዛኛው የካቢኔ አባል የክልሉ ማዕከላዊ ኮሚቴ ያኔ የለውጡ ጅምር አካባቢ የነበሩ ሰዎች ናቸው ነገር ግን በስራ ከኃላፊነት እንዲነሱ እና እንዲታገዱ ተደርጎ ነበር። ከአንድ አመት ተኩል ይሆናል።
አንዳንዶቹ የ #ኢዜማ እጩ ነበሩ የምርጫ አካባቢ፤ አሁን ትላንት ብቻ ነው በድንገት ያየናቸው እኛ ፓርቲ አባል ነን ብለው ፤ ከእኛ ጋር ከታገዱ እና ከስራ ከተነሱ ግማሹ ሁለት ዓመት ሆኖታል ግማሹ አንድ አመት ተኩል ፣ አንዳንዶቹ የሌላ ፓርቲ ዕጩ የነበሩ ናቸው።
ጉባኤ ላይ ውሳኔ የሚጠብቁ አሉ፤ እገዳ የተጣለባቸውም አሉ፤ አንዳንዶቹ ግን ጭራሽ አይመለከቱንም የኢዜማ እጩ የነበሩትን ዛሬ ላይ አባል ነው አይደለም ማለት ተገቢም አይመስለኝም "
አቶ ሲራጅ አደን (የሶማሌ ክልል የብልፅግና ፓርቲ አባል ነኝ ያሉ ሲሆን ፓርቲው ለሁለት መከፈሉን ይናገራሉ ) ፦
" የተፈጠረው የፓርቲው ለሁለት ተከፍሏል። የዚህ ምክንያት ያለ ግምገማ እና በብዛት በዝምድና እና በጋብቻ የተሳሰረ ስለሆነ ብዙ ጊዜ ህግ እና ደንብ አይከተልም በዛ ምክንያት ፓርቲው በሁለት በኩል ተከፍሏል።
አንድ ሰው ላይ በፓርቲ እርምጃ መውሰድ የሚቻለው በህግ እና ደንብ አሰራሩ ነው። ያለ ጉባኤ አንድ የአስፈፃሚ ኮሚቴ ወይም አንድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አንድ ሰው ውስኖ ከህግ ውጭ አንድን ሰው ከፓርቲ ውጭ ነው ማለት አይችልም በጉባኤ ነው የሚችለው።
የተፈጠረው የ12 አባላት የፓርቲው ማሀከለኛ እና ሁለት የአስፈፃሚ ኮሚቴ ለፌዴራል የፓርቲው ፅ/ቤት አዲስ አበባ ደብዳቤ በመፃፍ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል።
... ረብሻ አይደለም ህግ እና ደንቡን መከተል ነው። "
NB : የሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
ሁሉም አካላት ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ከሰጡት ቃል የተወሰደ።
@tikvahethiopia
በሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ምን ተፈጠረ ? ፓርቲው ለሁለት ተከፍሏል ?
የሶማሌ ክልል የኮሚኒኬሽን ምክትል ኃላፊ አቶ መሀመድ ሮብሌ ፦
" ... ከዚህ በፊት በተለያዩ ቦታ ተሰጥቷቸው በክልሉ በቢሮ ኃላፊ እና በምክትል ኃላፊነት ደረጃ የነበሩና ከዛ በኃላ በነበሩ ግድፈቶች እና ድክመቶች ስራቸውን በትክክል አለመስራት ፣ በሙስና፣ በተለያዩ ምክንያቶች ከስልጣን የተባረሩ ሰዎች ናቸው።
ተሰባስበው Issue ለመፍጠር ሲሉ ነው እንጂ በፓርቲው መሃል ምንም የተፈጠረ ችግር የለም።
እነዚህ Alredy ከሲስተም የወጡ ሰዎች ናቸው። ምናልባት አንዳንድ በትክክለኛ መንገድ ተገምግመው ያልተባረሩ ሰዎች እዛ ውስጥ ሊኖሩ ይችላሉ ፤ ሌላው ግን በትክክል ከሲስተም የወጡና ህብረተሰቡን ማገልገል ሳይችሉ ፣ የተሰጣቸውን ስራ መስራት ሳይችሉ ቀይርተው የተባረሩ ናቸው። "
የሶማሌ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የፅ/ቤት ኃላፊ እንጂነር መሀመድ ሻሌ ፦
" ... እኛም በሶሻል ሚዲያ ያየነው ነገር አለ። የነበረ ነገር ግን ከለውጡ ወዲህ የተለያዩ እርምጃዎች ሲወሰዱ ነበር ከስነምግባር እና ከሙስና ጋር በተያያዘ በዚህም ከስልጣን የተነሱ ሰዎች አሉ።
ትላንትና መግለጫ አውጥተዋል ተብለው በሶሻል ሚዲያ ያየኃቸው ሰዎች ነበሩ። አብዛኛው የካቢኔ አባል የክልሉ ማዕከላዊ ኮሚቴ ያኔ የለውጡ ጅምር አካባቢ የነበሩ ሰዎች ናቸው ነገር ግን በስራ ከኃላፊነት እንዲነሱ እና እንዲታገዱ ተደርጎ ነበር። ከአንድ አመት ተኩል ይሆናል።
አንዳንዶቹ የ #ኢዜማ እጩ ነበሩ የምርጫ አካባቢ፤ አሁን ትላንት ብቻ ነው በድንገት ያየናቸው እኛ ፓርቲ አባል ነን ብለው ፤ ከእኛ ጋር ከታገዱ እና ከስራ ከተነሱ ግማሹ ሁለት ዓመት ሆኖታል ግማሹ አንድ አመት ተኩል ፣ አንዳንዶቹ የሌላ ፓርቲ ዕጩ የነበሩ ናቸው።
ጉባኤ ላይ ውሳኔ የሚጠብቁ አሉ፤ እገዳ የተጣለባቸውም አሉ፤ አንዳንዶቹ ግን ጭራሽ አይመለከቱንም የኢዜማ እጩ የነበሩትን ዛሬ ላይ አባል ነው አይደለም ማለት ተገቢም አይመስለኝም "
አቶ ሲራጅ አደን (የሶማሌ ክልል የብልፅግና ፓርቲ አባል ነኝ ያሉ ሲሆን ፓርቲው ለሁለት መከፈሉን ይናገራሉ ) ፦
" የተፈጠረው የፓርቲው ለሁለት ተከፍሏል። የዚህ ምክንያት ያለ ግምገማ እና በብዛት በዝምድና እና በጋብቻ የተሳሰረ ስለሆነ ብዙ ጊዜ ህግ እና ደንብ አይከተልም በዛ ምክንያት ፓርቲው በሁለት በኩል ተከፍሏል።
አንድ ሰው ላይ በፓርቲ እርምጃ መውሰድ የሚቻለው በህግ እና ደንብ አሰራሩ ነው። ያለ ጉባኤ አንድ የአስፈፃሚ ኮሚቴ ወይም አንድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አንድ ሰው ውስኖ ከህግ ውጭ አንድን ሰው ከፓርቲ ውጭ ነው ማለት አይችልም በጉባኤ ነው የሚችለው።
የተፈጠረው የ12 አባላት የፓርቲው ማሀከለኛ እና ሁለት የአስፈፃሚ ኮሚቴ ለፌዴራል የፓርቲው ፅ/ቤት አዲስ አበባ ደብዳቤ በመፃፍ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል።
... ረብሻ አይደለም ህግ እና ደንቡን መከተል ነው። "
NB : የሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
ሁሉም አካላት ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ከሰጡት ቃል የተወሰደ።
@tikvahethiopia
#EZEMA
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ ( #ኢዜማ ) በመጪው ሰኔ 11 እና 12 / 2014 ዓ/ም ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሂዳል በዚህም ፓርቲውን በመሪነት እና በሊቀመንበርነት የሚመሩ አመራሮችን እንደሚመርጥ አስታውቋል።
ፓርቲው ይህን ያሳውቀው ዛሬ በዋና ፅ/ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው።
ዕጩ አመራሮቹ ከጠቅላላ ጉባኤው መዳረሻ በፊት ለ19 ቀናት የምረጡኝ ቅስቀሳ እንደሚያደርጉ ፓርቲው ገልጿል።
ኢዜማ ጠቅላላ ጉባኤ የጠራው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ በሚደነግገው መሰረት በሶስት ዓመት አንዴ መደበኛ ጉባኤ ማከናወን ስለሚገባው መሆኑን አመልክቷል።
በመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው የኢዜማ መሪ፣ ምክትል መሪ፣ ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር፣ ዋና ጸሐፊ እና የፓርቲው የፋይናንስ ክፍል ኃላፊ እንደሚመረጡ ፓርቲው ይፋ አድርጓል።
በግንቦት 2011 የተመሰረተው ኢዜማን ላለፉት ሶስት ዓመታት በመሪነት እያገለገሉ የሚገኙት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሲሆኑ የምክትል መሪነት ስልጣን ያላቸው ደግሞ አቶ አንዷለም አራጌ ናቸው።
የኢዜማን የዕለት ተዕለት ስራ በሙሉ ጊዜ የመምራት ኃላፊነት የተሰጠው ለፓርቲው ሊቀመንበር ነው።
አቶ የሺዋስ አሰፋ የኢዜማ ሊቀመንበርነት ኃላፊነትን ተረክበው ፓርቲውን እየመሩ የሚገኙ ሲሆን ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው የምክትል ሊቀመንበርነት ቦታውን ይዘው ቆይተዋል።
ኢዜማን በአሁኑ ወቅት በዋና ጸሐፊነት በማገልገል ላይ የሚገኙት አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ ( #ኢዜማ ) በመጪው ሰኔ 11 እና 12 / 2014 ዓ/ም ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሂዳል በዚህም ፓርቲውን በመሪነት እና በሊቀመንበርነት የሚመሩ አመራሮችን እንደሚመርጥ አስታውቋል።
ፓርቲው ይህን ያሳውቀው ዛሬ በዋና ፅ/ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው።
ዕጩ አመራሮቹ ከጠቅላላ ጉባኤው መዳረሻ በፊት ለ19 ቀናት የምረጡኝ ቅስቀሳ እንደሚያደርጉ ፓርቲው ገልጿል።
ኢዜማ ጠቅላላ ጉባኤ የጠራው የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ በሚደነግገው መሰረት በሶስት ዓመት አንዴ መደበኛ ጉባኤ ማከናወን ስለሚገባው መሆኑን አመልክቷል።
በመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው የኢዜማ መሪ፣ ምክትል መሪ፣ ሊቀመንበር፣ ምክትል ሊቀመንበር፣ ዋና ጸሐፊ እና የፓርቲው የፋይናንስ ክፍል ኃላፊ እንደሚመረጡ ፓርቲው ይፋ አድርጓል።
በግንቦት 2011 የተመሰረተው ኢዜማን ላለፉት ሶስት ዓመታት በመሪነት እያገለገሉ የሚገኙት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሲሆኑ የምክትል መሪነት ስልጣን ያላቸው ደግሞ አቶ አንዷለም አራጌ ናቸው።
የኢዜማን የዕለት ተዕለት ስራ በሙሉ ጊዜ የመምራት ኃላፊነት የተሰጠው ለፓርቲው ሊቀመንበር ነው።
አቶ የሺዋስ አሰፋ የኢዜማ ሊቀመንበርነት ኃላፊነትን ተረክበው ፓርቲውን እየመሩ የሚገኙ ሲሆን ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው የምክትል ሊቀመንበርነት ቦታውን ይዘው ቆይተዋል።
ኢዜማን በአሁኑ ወቅት በዋና ጸሐፊነት በማገልገል ላይ የሚገኙት አቶ አበበ አካሉ ናቸው።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ከፍተኛ አመራሮችን ለመምረጥ ሚስጥራዊ የድምፅ አሰጣጥ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ፓርቲውን ለመምራት እየተወዳደሩ የሚገኙት እጩዎች ባለፉት ሳምንታት ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበረ ሲሆን ዛሬ የመጨረሻው ውጤት የሚለይበት ነው። በተለይም ደግሞ ለፓርቲው መሪነት የሚወዳደሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ አንዱአለም አራጌ ውጤትን በርካታ የፓርቲው ደጋፊዎች…
#ኢዜማ
የኢዜማ የአመራሮች ምርጫ ውጤት እስካሁን (ምሽት 4:18 ድረስ) ይፋ ያልሆነ ሲሆን ፓርቲው ቆጠራው እንደተጠናቀቀ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
የጉባኤው አባላት የአመራሮችን ምርጫ ውጤት እየተጠባበቁ ይገኛሉ።
ተከታትለን እናሳውቃለን !
@tikvahethiopia
የኢዜማ የአመራሮች ምርጫ ውጤት እስካሁን (ምሽት 4:18 ድረስ) ይፋ ያልሆነ ሲሆን ፓርቲው ቆጠራው እንደተጠናቀቀ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
የጉባኤው አባላት የአመራሮችን ምርጫ ውጤት እየተጠባበቁ ይገኛሉ።
ተከታትለን እናሳውቃለን !
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢዜማ የኢዜማ የአመራሮች ምርጫ ውጤት እስካሁን (ምሽት 4:18 ድረስ) ይፋ ያልሆነ ሲሆን ፓርቲው ቆጠራው እንደተጠናቀቀ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል። የጉባኤው አባላት የአመራሮችን ምርጫ ውጤት እየተጠባበቁ ይገኛሉ። ተከታትለን እናሳውቃለን ! @tikvahethiopia
#NewsAlert #ኢዜማ
ፕሮፌሰር ብርሃኑ መሪ ፤ አርክቴክት ዮሐንስ ደግሞ ምክትል መሪ ሆነው ተመረጡ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ምርጫ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋን እና አርክቴክት ዮሐንስ መኮንንን የኢዜማ #መሪ እና #ምክትል_መሪ አድርጎ መርጧል፡፡
በጉባኤው ላይ ወደ 900 ገደማ የፓርቲው አባላት ያተሳተፉ ሲሆን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ 549 ድምፅ ማግኘታቸው ተገልጿል።
ከፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ጋር ለመሪነት የተወዳደሩት አቶ አንዱአለም አራጌ 326 ድምፅ ነው ያገኙት። አቶ አንዱአለም ከፓርቲው ምስረታ አንስቶ የፓርቲው ምክትል መሪ ሆነው ቆይተዋል።
ለምክትል መሪነት የተወዳደሩት አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን በጉባኤው የተመረጡ ሲሆን ለቦታው በተፎካካሪነት ቀርበው የነበሩት አቶ ሀብታሙ ኪታባ ነበሩ።
@tivahethiopia
ፕሮፌሰር ብርሃኑ መሪ ፤ አርክቴክት ዮሐንስ ደግሞ ምክትል መሪ ሆነው ተመረጡ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ምርጫ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋን እና አርክቴክት ዮሐንስ መኮንንን የኢዜማ #መሪ እና #ምክትል_መሪ አድርጎ መርጧል፡፡
በጉባኤው ላይ ወደ 900 ገደማ የፓርቲው አባላት ያተሳተፉ ሲሆን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ 549 ድምፅ ማግኘታቸው ተገልጿል።
ከፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ጋር ለመሪነት የተወዳደሩት አቶ አንዱአለም አራጌ 326 ድምፅ ነው ያገኙት። አቶ አንዱአለም ከፓርቲው ምስረታ አንስቶ የፓርቲው ምክትል መሪ ሆነው ቆይተዋል።
ለምክትል መሪነት የተወዳደሩት አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን በጉባኤው የተመረጡ ሲሆን ለቦታው በተፎካካሪነት ቀርበው የነበሩት አቶ ሀብታሙ ኪታባ ነበሩ።
@tivahethiopia
#አብን #ኢዜማ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገራዊ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የመጀመሪያ ዙር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ላይ አስታውቀዋል።
በቀጣይም #በሚያግባቡ_ሀገራዊ_ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና #የጋራ_አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ መደረሳቸውንም ገልፀዋል።
ሁለቱ ፓርቲዎች የ " ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት " ን ከሽብርተኝነት መዝገብ መሰረዝን በቅድሚያ የተቃወሙ ፓርቲዎች ናቸው።
ፓርቲዎቹ ተቃውሟቸውን በየተናጠል ባወጡት በመግለጫ አሳውቀዋል።
ይህ ከተሰማ ከሰዓታት በኃላ ነው ሁለቱ ፓርቲዎች በሚያግባቡ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና የጋራ አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ እንደደረሱ የተነገረው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገራዊ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የመጀመሪያ ዙር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ላይ አስታውቀዋል።
በቀጣይም #በሚያግባቡ_ሀገራዊ_ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና #የጋራ_አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ መደረሳቸውንም ገልፀዋል።
ሁለቱ ፓርቲዎች የ " ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት " ን ከሽብርተኝነት መዝገብ መሰረዝን በቅድሚያ የተቃወሙ ፓርቲዎች ናቸው።
ፓርቲዎቹ ተቃውሟቸውን በየተናጠል ባወጡት በመግለጫ አሳውቀዋል።
ይህ ከተሰማ ከሰዓታት በኃላ ነው ሁለቱ ፓርቲዎች በሚያግባቡ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና የጋራ አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ እንደደረሱ የተነገረው።
@tikvahethiopia
#ኢዜማ
ጉምቱው ፖለቲከኛ ከፓርቲያቸው ለቀቁ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መስራቾች አንዱ የሆኑት ጉምቱው ፖለቲከኛ አቶ አንዱዓለም አራጌ ከፓርቲው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።
የመልቀቂያ ደብዳቤው በትላንትናው እለት ለሚመለከተው አካል ገቢ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
አቶ አንዱዓለም አራጌ ፓርቲውን ለምን ለቀቁ ? የመልቀቂያ ደብዳቤያቸው ላይ በዝርዝር አስረድተዋል ፤ ከላይ ተያይዟል ያንብቡት !
ምንጭ፦ የተረጋገጠው የማህበራዊ ትስድር ገፃቸው
@tikvahethiopia
ጉምቱው ፖለቲከኛ ከፓርቲያቸው ለቀቁ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መስራቾች አንዱ የሆኑት ጉምቱው ፖለቲከኛ አቶ አንዱዓለም አራጌ ከፓርቲው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።
የመልቀቂያ ደብዳቤው በትላንትናው እለት ለሚመለከተው አካል ገቢ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
አቶ አንዱዓለም አራጌ ፓርቲውን ለምን ለቀቁ ? የመልቀቂያ ደብዳቤያቸው ላይ በዝርዝር አስረድተዋል ፤ ከላይ ተያይዟል ያንብቡት !
ምንጭ፦ የተረጋገጠው የማህበራዊ ትስድር ገፃቸው
@tikvahethiopia