ፈይሳ ሌሊሳ ተሸለመ🔝
ከሁለት አመታት በፊት በሪዮ ኦሎምፒክ እጆቹን ከፍ አድርጎ በማጣመር የኢትዮጵያ መንግሥት በወቅቱ #በተቃዋሚዎች ላይ ይወስድ የነበረውን የኃይል እርምጃ #የተቃወመው ፈይሳ ሌሊሳ በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሽልማት ተበረከተለት። ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ለፈይሳ ሽልማቱ የተበረከተለት በሪዮ ኦሎምፒክ የማራቶን ውድድር #ሁለተኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ በማስገኘቱ ነው።
Photo: #PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከሁለት አመታት በፊት በሪዮ ኦሎምፒክ እጆቹን ከፍ አድርጎ በማጣመር የኢትዮጵያ መንግሥት በወቅቱ #በተቃዋሚዎች ላይ ይወስድ የነበረውን የኃይል እርምጃ #የተቃወመው ፈይሳ ሌሊሳ በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሽልማት ተበረከተለት። ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ለፈይሳ ሽልማቱ የተበረከተለት በሪዮ ኦሎምፒክ የማራቶን ውድድር #ሁለተኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ በማስገኘቱ ነው።
Photo: #PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"መኖር ማለት አለመሞት ከሆነ እስትንፋስ ያለው ሁሉ እየኖረ ነው። ግን መኖር ማለት እራስን መሆን፣ ለዓላማ መቆም፣ ህሊናን አለመዘንጋት፣ ፍርድን አለማጓደል፣ ለራስ ብቻ ሳይሆን ለሌላው እራስን መስዋዕት ማድረግ ብሎም አርአያ የሚሆን ነገር ጥሎ ማለፍ ከሆነ ስንቶቻችን ነን በህይወት ያለነው?" ዶክተር #ምህረት_ደበበ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሰሜን ሸዋ ግጭት እንዲከሰት ያደረጉ አካላት ለህግ እንዲቀርቡ እንሰራለን - ኦዲፒ
በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደርና በሰሜን ሸዋ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች ግጭት እንዲከሰት ያደረጉ አካላት ለህግ እንዲቀርቡ እንደሚሰራ የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) አስታውቋል፡፡
ኦዲፒ የተፈጠረዉን ችግር ለማረጋጋት እና ተመሳሳይ ችግር ዳግም እንዳይከሰት ለማድረግ ከአማራ ክልል መንግስት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ በግጭቱ ህይወታቸውን ባጡ ቤተሰቦች የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethopia
በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደርና በሰሜን ሸዋ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች ግጭት እንዲከሰት ያደረጉ አካላት ለህግ እንዲቀርቡ እንደሚሰራ የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) አስታውቋል፡፡
ኦዲፒ የተፈጠረዉን ችግር ለማረጋጋት እና ተመሳሳይ ችግር ዳግም እንዳይከሰት ለማድረግ ከአማራ ክልል መንግስት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ በግጭቱ ህይወታቸውን ባጡ ቤተሰቦች የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethopia
#Update የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ሜጀር ጄኔራል ደግፌ በዲ ከኃላፊነታቸው ተነሱ። ኮሚሽኑንን ከዘጠኝ ወራት በላይ በሃላፊነት ሲመሩ የቆዩት ሜጀር ጄኔራል ደግፌ በዲ መነሳታቸው ተገልጿል፡፡
ኮሚሽነሩ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ሰኔ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ነበር
የኮሚሽኑን የቀድሞ ሃላፊ አቶ ይህደጎ ሥዩምን ተክተው የተሾሙት።
ሜጀር ጄኔራል ደግፌ፣ ከኃላፊነታቸው በድንገት የተነሱበት ዝርዝር ምክንያት ለጊዜው ባይታወቅም፣ ማክሰኞ ሚያዝያ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. የደረሳቸው የስንብት ደብዳቤ ግን ‹‹በጡረታ›› የሚል መሆኑ ታውቋል፡፡
ላለፉት ዘጠኝ ወራት ኮሚሽኑን ሲመሩ ቆይተው፣ ከሚያዝያ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በጡረታ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል፡፡
Via Reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኮሚሽነሩ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ሰኔ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. ነበር
የኮሚሽኑን የቀድሞ ሃላፊ አቶ ይህደጎ ሥዩምን ተክተው የተሾሙት።
ሜጀር ጄኔራል ደግፌ፣ ከኃላፊነታቸው በድንገት የተነሱበት ዝርዝር ምክንያት ለጊዜው ባይታወቅም፣ ማክሰኞ ሚያዝያ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. የደረሳቸው የስንብት ደብዳቤ ግን ‹‹በጡረታ›› የሚል መሆኑ ታውቋል፡፡
ላለፉት ዘጠኝ ወራት ኮሚሽኑን ሲመሩ ቆይተው፣ ከሚያዝያ 1 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በጡረታ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል፡፡
Via Reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የጣሊያን መከላከያ ሚኒስትር ኤልዛቤታ ቴራንታ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ነው። ሚኒስትሯ ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ሲገቡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በዛሬው እለትም በእርሳቸው ከሚመራው የልዑካን ቡድን ጋር በመሆን ከኢንጂነር አይሻና ከመከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር ይወያያሉ። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ ጉዳይ ላይ የሚመክሩ ሲሆን፥ የትብብር ስምምነቶችን እንደሚፈራረሙም ከመከላከያ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
Via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሱዳን ፖሊስ አባላት ተቃዋሚ ሰልፈኞች ላይ እርምጃ እንዳይወስድ ታዘዙ‼️
.
.
የሱዳን ፖሊስ በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚ ሰልፈኞች ላይ ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስድ አባላቱን አዘዘ።
ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ከአርብ ዕለት ጀምሮ በጦር ኃይሉ ዋና መስሪያ ቤት ፊት ለፊት በመገኘት ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው።
ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ፕሬዝዳንት ኦማር አል በሺር ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቁ ናቸው።
ቀደም ብሎ ከዋና መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውጪ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ የተሰማ ሲሆን ይህ የሆነውም ወታደሮች ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ላይ የመንግሥት የደህንነት ኃይሎች እንዳይተኩሱባቸው ሲከላከሉ እንደሆነ ተሰምቷል።
የፖሊስ ቃል አቀባይ ባወጣው መግለጫ "ሁሉንም አባላቱን ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ እንዳይተኩሱ ታዟል።" ብሏል።
"ፈጣሪ ሀገራችንን እንዲያረጋጋ እና ደህንነታችን እንዲጠብቅ .... ሱዳናውያን አንድ እንዲያደርገን....ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር መግባባት ላይ እንድንደርስ እንፀልያለን"ብለዋል በመግለጫቸው።
ከዚህ ቀደም ሰላማዊ ሰልፈኞቹን ለመበተን የሞከሩ የብሄራዊ ፀጥታና ደህንነት አባላት ከወታደሩ ጋር መጋጨታቸው ተዘግቧል።
የተቃውሞ ሰልፉ ከተጀመረ ቢያንስ ሁለት ወታደሮች ከዋና መስሪያ ቤቱ ውጪ መሞታቸው ተዘግቧል።
የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰባት ተቃዋሚ ሰልፈኞች መሞታቸውን 15 መጎዳታቸውን እና 42 የደህንነት ኃይሎች መጎዳታቸውን ገልፀው ነበር።
2ሺህ አምስት መቶ ሰዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል።
ከተቃዋሚ ሰልፈኞቹ አንዱ ለቢቢሲ እንደገለፀው ሰልፉን ለመበተን አስለቃሽ ጋዝ፣ ጥይት በደህንነት ኃይሎች ተተኩሷል።
ወታደሮችም ተቃዋሚ ሰልፈኞችን በግቢያቸው እንዲደበቁ እንደረዷቸው ተናግሯል።
አክሎም "ኦማር አል በሺር ተቃዋሚ ሰልፈኞቹን ከአደባባዮች ላይ ዞር እንዲሉ ለማድረግ መሞከራቸው እርባና ቢስ ነው ምክንያቱም የትም አንሄድም " ብሏል።
ሌላ ተቃዋሚ ሰልፈኛ በበኩሉ ሁሉም የመከላከያ እና የፖሊስ አባላት ተቃዋሚ ሰልፈኞቹን እንደማይደግፉ ገልጧል።
ከፍተኛ ሹማምንቶቹ አሁንም ፕሬዝዳንቱን የሚደግፉ ሲሆን አነስተኛ ማዕረግ ያላቸውና ተራው ወታደርና አባል ግን ከሕዝቡ ጋር ነው ሲል ለቢቢሲ አስረድቷል።
አሜሪካ፣ እንግሊዝና ናርዌይ ሱዳን የፖለቲካ ሽግግር ለማድረግ መዘጋጀት እንዳለበት ገልፀዋል።
Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
የሱዳን ፖሊስ በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚ ሰልፈኞች ላይ ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስድ አባላቱን አዘዘ።
ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ከአርብ ዕለት ጀምሮ በጦር ኃይሉ ዋና መስሪያ ቤት ፊት ለፊት በመገኘት ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው።
ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ፕሬዝዳንት ኦማር አል በሺር ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቁ ናቸው።
ቀደም ብሎ ከዋና መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውጪ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ የተሰማ ሲሆን ይህ የሆነውም ወታደሮች ተቃዋሚ ሰልፈኞቹ ላይ የመንግሥት የደህንነት ኃይሎች እንዳይተኩሱባቸው ሲከላከሉ እንደሆነ ተሰምቷል።
የፖሊስ ቃል አቀባይ ባወጣው መግለጫ "ሁሉንም አባላቱን ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ እንዳይተኩሱ ታዟል።" ብሏል።
"ፈጣሪ ሀገራችንን እንዲያረጋጋ እና ደህንነታችን እንዲጠብቅ .... ሱዳናውያን አንድ እንዲያደርገን....ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር መግባባት ላይ እንድንደርስ እንፀልያለን"ብለዋል በመግለጫቸው።
ከዚህ ቀደም ሰላማዊ ሰልፈኞቹን ለመበተን የሞከሩ የብሄራዊ ፀጥታና ደህንነት አባላት ከወታደሩ ጋር መጋጨታቸው ተዘግቧል።
የተቃውሞ ሰልፉ ከተጀመረ ቢያንስ ሁለት ወታደሮች ከዋና መስሪያ ቤቱ ውጪ መሞታቸው ተዘግቧል።
የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰባት ተቃዋሚ ሰልፈኞች መሞታቸውን 15 መጎዳታቸውን እና 42 የደህንነት ኃይሎች መጎዳታቸውን ገልፀው ነበር።
2ሺህ አምስት መቶ ሰዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል።
ከተቃዋሚ ሰልፈኞቹ አንዱ ለቢቢሲ እንደገለፀው ሰልፉን ለመበተን አስለቃሽ ጋዝ፣ ጥይት በደህንነት ኃይሎች ተተኩሷል።
ወታደሮችም ተቃዋሚ ሰልፈኞችን በግቢያቸው እንዲደበቁ እንደረዷቸው ተናግሯል።
አክሎም "ኦማር አል በሺር ተቃዋሚ ሰልፈኞቹን ከአደባባዮች ላይ ዞር እንዲሉ ለማድረግ መሞከራቸው እርባና ቢስ ነው ምክንያቱም የትም አንሄድም " ብሏል።
ሌላ ተቃዋሚ ሰልፈኛ በበኩሉ ሁሉም የመከላከያ እና የፖሊስ አባላት ተቃዋሚ ሰልፈኞቹን እንደማይደግፉ ገልጧል።
ከፍተኛ ሹማምንቶቹ አሁንም ፕሬዝዳንቱን የሚደግፉ ሲሆን አነስተኛ ማዕረግ ያላቸውና ተራው ወታደርና አባል ግን ከሕዝቡ ጋር ነው ሲል ለቢቢሲ አስረድቷል።
አሜሪካ፣ እንግሊዝና ናርዌይ ሱዳን የፖለቲካ ሽግግር ለማድረግ መዘጋጀት እንዳለበት ገልፀዋል።
Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላም...
ካለፈው አርብ ዕለት ጀምራ ላለፉት ሁለት ቀናት አንፃራዊ የሰላም እጥረት አጋጥሟት የነበረችው ደሴ ወደ ቀድሞ #ሰላሟ ተመልሳለች፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ካለፈው አርብ ዕለት ጀምራ ላለፉት ሁለት ቀናት አንፃራዊ የሰላም እጥረት አጋጥሟት የነበረችው ደሴ ወደ ቀድሞ #ሰላሟ ተመልሳለች፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ሕዝቡ ወደቀየው #መመለስ ጀምሯል፤ ግን ሰብዓዊ ድጋፍ ያስፈልጋል፡፡››
‹‹ችግሩን ለመፍጠር ካስፈለገው ምክንያት አንፃር ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን መንግሥት ኃላፊነት ወስዶ ሊሠራልን ይገባል፡፡›› የአጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራቆሬ ነዋሪዎች
.
.
.
ሰሞኑን በሰሜን ሽዋ ዞን አጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራ ቆሬ አካባቢዎች በተፈጠረ ግጭት የሰው ሕይወት እና ንብረት ጠፍቷል፡፡ በችግሩም ከቀያቸው ውጭ የተሰደዱ ዜጎች እንዳሉ አብመድ ከአካባቢዎቹ ነዋሪዎች አረጋግጧል፡፡
በአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊው አቶ ሰለሞን አልታየ ከትናንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ ረፋዱ ድረስ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ዳግም በከተማዋ መኖሩን ተናግረዋል፡፡ ‹‹በግጭት ስጋት ከቀያቸው ሸሽተው የነበሩ ወገኖቻችንም መመለስ ጀምረዋል›› ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ዜጎቹ ቢመለሱም ሀብት ንብረታቸው በመዘረፉ ለዕለት ሊበሉ የሚችሉት እንኳ ባለመኖሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ አለኝታነቱን እንዲያሳይ እጠይቃለሁ ነው ያሉት፡፡ በአከባቢው የመከላከያ ሠራዊት ሰላም የማስጠበቅ ሥራ እየሠራ ነው፤ በዘላቂነት ከሚነሳው እና ከሚታየው ሐሳብ አንፃር የቀጠናውን ሰላም ለማስጠበቅ እና ከመሰል ድርጊቶች ለመጠበቅ የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ በአቅራቢያው ሊኖር እንደሚገባም አቶ ሰሎሞን ተናረዋል፡፡
በማጀቴ ከተማ ውስጥ በሕመም ምክንያት ከመንደራቸው እንዳልወጡ የነገሩን ወይዘሮ ፋጤ ደሳለኝ ከትናንት ጀምሮ እስከ ርፋዱ ድረስ ያለው የአካባቢው ሁኔታ ሰላማዊእደሆነ ነግረውናል፡፡ ሕዝቡም ሰላማዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን ነው የገለጹልን፡፡
የካራ ቆሬ ነዋሪው አቶ ደንበሬ ገብረማሪያም ደግሞ ‹‹ከትናንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ 5፡30 ድረስ አካባቢው ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ነው፡፡ የመከላከያ ሠራዊትም እየተዘዋወሩ ሰላማችን እየጠበቁልን ነው፡፡ ሕዝቡም ስለ አጥፊዎቹ ሙሉ መረጃ ለመስጠት ዝግጁ ነው›› ብለዋል፡፡ አቶ ደንበሩ ከተለያዩ አጎራባች ከተሞች እና በየተራራው የነበሩ ዜጎች እየተመለሱ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን የተመላሾቹ መኖሪያ ቤት እና የንግድ ተቋማት ሙሉ በሙሉ በግጭቱ ቀናት በመዘረፉ እና በመውደሙ የዕለት ጉርስ የላቸውም፤ እነዚህን በዘላቂነት ለማቋቋም መንግሥት እና የኢትዮጵያ ሕዝብ አስቸኳይ ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል›› ብለዋል፡፡
ችግሩን ለመፍጠር ካስፈለገው ምክንያት አንፃር ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን መንግሥት ኃላፊነት ወስዶ ሊሠራልን ይገባልም ብለዋል አቶ ደንበሩ፡፡
በከተማዋ ግጭት ለፈጠሩ ኃይሎች መረጃ አቀባዮች በመኖራቸው የአካባቢው ሕዝብ ወደመደበኛ ሥራው ለመመለስ በመቸገሩ አጥፊዎችን የመያዝ እና ዘላቂ ሰላም እንዲፈጠር የማድረግ ኃላፊነት ወስዶ መንግሥት ሊሠራ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ችግሩን ለመፍጠር ካስፈለገው ምክንያት አንፃር ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን መንግሥት ኃላፊነት ወስዶ ሊሠራልን ይገባል፡፡›› የአጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራቆሬ ነዋሪዎች
.
.
.
ሰሞኑን በሰሜን ሽዋ ዞን አጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራ ቆሬ አካባቢዎች በተፈጠረ ግጭት የሰው ሕይወት እና ንብረት ጠፍቷል፡፡ በችግሩም ከቀያቸው ውጭ የተሰደዱ ዜጎች እንዳሉ አብመድ ከአካባቢዎቹ ነዋሪዎች አረጋግጧል፡፡
በአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊው አቶ ሰለሞን አልታየ ከትናንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ ረፋዱ ድረስ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ዳግም በከተማዋ መኖሩን ተናግረዋል፡፡ ‹‹በግጭት ስጋት ከቀያቸው ሸሽተው የነበሩ ወገኖቻችንም መመለስ ጀምረዋል›› ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ዜጎቹ ቢመለሱም ሀብት ንብረታቸው በመዘረፉ ለዕለት ሊበሉ የሚችሉት እንኳ ባለመኖሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ አለኝታነቱን እንዲያሳይ እጠይቃለሁ ነው ያሉት፡፡ በአከባቢው የመከላከያ ሠራዊት ሰላም የማስጠበቅ ሥራ እየሠራ ነው፤ በዘላቂነት ከሚነሳው እና ከሚታየው ሐሳብ አንፃር የቀጠናውን ሰላም ለማስጠበቅ እና ከመሰል ድርጊቶች ለመጠበቅ የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ በአቅራቢያው ሊኖር እንደሚገባም አቶ ሰሎሞን ተናረዋል፡፡
በማጀቴ ከተማ ውስጥ በሕመም ምክንያት ከመንደራቸው እንዳልወጡ የነገሩን ወይዘሮ ፋጤ ደሳለኝ ከትናንት ጀምሮ እስከ ርፋዱ ድረስ ያለው የአካባቢው ሁኔታ ሰላማዊእደሆነ ነግረውናል፡፡ ሕዝቡም ሰላማዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን ነው የገለጹልን፡፡
የካራ ቆሬ ነዋሪው አቶ ደንበሬ ገብረማሪያም ደግሞ ‹‹ከትናንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ 5፡30 ድረስ አካባቢው ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ነው፡፡ የመከላከያ ሠራዊትም እየተዘዋወሩ ሰላማችን እየጠበቁልን ነው፡፡ ሕዝቡም ስለ አጥፊዎቹ ሙሉ መረጃ ለመስጠት ዝግጁ ነው›› ብለዋል፡፡ አቶ ደንበሩ ከተለያዩ አጎራባች ከተሞች እና በየተራራው የነበሩ ዜጎች እየተመለሱ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን የተመላሾቹ መኖሪያ ቤት እና የንግድ ተቋማት ሙሉ በሙሉ በግጭቱ ቀናት በመዘረፉ እና በመውደሙ የዕለት ጉርስ የላቸውም፤ እነዚህን በዘላቂነት ለማቋቋም መንግሥት እና የኢትዮጵያ ሕዝብ አስቸኳይ ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል›› ብለዋል፡፡
ችግሩን ለመፍጠር ካስፈለገው ምክንያት አንፃር ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን መንግሥት ኃላፊነት ወስዶ ሊሠራልን ይገባልም ብለዋል አቶ ደንበሩ፡፡
በከተማዋ ግጭት ለፈጠሩ ኃይሎች መረጃ አቀባዮች በመኖራቸው የአካባቢው ሕዝብ ወደመደበኛ ሥራው ለመመለስ በመቸገሩ አጥፊዎችን የመያዝ እና ዘላቂ ሰላም እንዲፈጠር የማድረግ ኃላፊነት ወስዶ መንግሥት ሊሠራ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ🚍በዚህ ሳምንት ቅዳሜና እሁድ(ሚያዚያ 5 እና ሚያዚያ 6) #StopHateSpeech
ተዘጋጁ!!
#ሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ ----- ሚያዚያ 12 እና 13
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተዘጋጁ!!
#ሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ ----- ሚያዚያ 12 እና 13
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በቢሾፍቱ አቅራቢያ የዛሬ አንድ ወር በተከሰሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ ህይወታቸውን ላጡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሰራተኞች ዛሬ የመታሰቢያ ስነ ስርዓት በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የመታሰቢያ ስነ ስርዓቱ የተከናወነው በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ ውስጥ ነው።
Via DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia