TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል #ልዩነትንና #መከፋፈልን ለመፍጠር በተለያየ መንገድ የሚደረገውን አፍራሽ እንቅስቃሴ መላው ዜጋ በጋራ መታገል አለበት ሲሉ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት አቶ #ለማ_መገረሳ ተናገሩ። አቶ ለማ ይህንን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓብይ አህመድ በተገኙበት ከቡኖ በደሌ ዞን ነዋሪዎች ጋር በበደሌ ከተማ ዛሬ በተካሄደው ውይይት ላይ ነው። በዚሁ ወቅት አቶ ለማ የኦሮሞ ህዝብ ኢትዮጵያን ለመገንባት ከፍተኛ መስዋእትነት ከፍሏል፤ በአሁኑ ወቅትም አንድነቷን አስጠብቆ ለማቆየት ከሌሎች ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ ይሰራል ብለዋል። “የኦሮሞ ህዝብ የኢትዮጵያን አንድነት የማስጠበቅ ግዴታ አለበት” ሲሉም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia