TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.08K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ማሳሰቢያ

በያዝነው ክረምት በተከዜ ወንዝ ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድባችን እየገባ ያለው የውኃ መጠን የሞላ በመሆኑ ለግድቡ ደህንነት ሲባል የውኃውን መጠን ከነሐሴ 18 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ መቀነስ አስፈልጓል፡፡

ስለሆነም ከግድቡ በታችኛው እና በላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች ማለትም በትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መስተዳድር በመሃከለኛው ዞን የሚገኙ ወረዳዎች ማለትም በጣንቋአበርገሌ፣ በቆላ ተንቤን፣ በላዕላይማይጨው፣ በታህታይ ማይጨው፣ በመረብ ለሄ በሰሜን ምዕራባዊ ዞን ደግሞ በአሰገደ ጺምበላ፣ በላዕላይ አዲያቦ፣ በመደባይ ዛና፣ በታህታይ አዲያቦ፣ በታህታይ ኾራሮ፣ በፀለምቲ እንዲሁም በምዕራባዊ ዞን በካፍታ ሁመራ፣ በፀገዴ፣ በወልቃይት በተያያዘ ሁኔታም በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መስተዳድር በዋግኽምራ ዞን ስር በአበርገሌ ወረዳ፣ በሰሜን ጎንደር ዞን በፀለምት ወረዳ በአጠቃላይ የተከዜ ወንዝ አዋሳኝ ቀበሌዎች እና በአካባቢው ነዋሪ ህዝቦች ከወዲሁ ይህንኑ #በመገንዘብ በሰውም ሆነ በእንሰሳት ላይ በሚለቀቀው #ደራሽ ውሃ #ጉዳት እንዳይደርስ ተገቢውን #ጥንቃቄ ታደርጉ ዘንድ በአክብሮት ለማሳሰብ ይወዳል፡፡

📌ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia